Sider

lørdag 20. juli 2013

በቦንድ ሽያጭ ያልተሳካው የገንዘብ ዘረፋ በኮንደሚኒየም ሰበብ መሳካት የለበትም!!!

ወያኔ በጠመንጃ ኃይል ሥልጣን ከተቆጣጠረበት 1983 ጀምሮ በከተሞች አካባቢ ምንም አይነት ሕዝባዊ ተቀባይነት ኖሮት አያውቅም። ለዚህም የሚሰጠው ምክንያት ከተሞች በጠላትነት በተፈረጀው አማራና የቀድሞ ሥርዓት ናፋቂዎች የተሞሉ ስለሆነ ነው ይላል። ዋና ከተማችን አዲስ አበባ በዚህ ውንጀላ ዋጋ ከከፈሉት ከተሞች ግንባር ቀደሟ ናት። በተለይ በመጀመሪያው የወያኔ 10 (አሥር) የሥልጣን አመታት የከተማዋን የነዋሪዎች አሰፋፈር ስብጥር ሆን ብሎ ለመቀየር ከመሞከር ጀምሮ የተለያዩ የአገልግሎት መስጫ ተቋሞችን አቅም ለማዳከም በርካታ አሳዛኝ እርምጃዎች ተወስደዋል።
ታሪክን ወደኋላ መለስ ብለን እንቃኝ። የፋሺስት ጣልያን ጦር በእንግሊዝ ጦር ትብብር በኢትዮጵያ አርበኞች ከተደመሰሰ በኋላ በአሸናፊነው ወደከተሞች የገባው የእንግሊዝ ጦር ያገኘውን ንብረት በወቅቱ የቅኝ ግዛቶቹ ወደ ነበሩት ኬንያና ሱማሌ አሽሽቷል። ከብዙ ዓስርተ ዓመታት በኋላ ወያኔ ይህንኑ እኩይ ተግባር ደገመው። ወያኔ በያዛቸው ከተሞች ውስጥ ያገኘኛቸውን ውድ ዋጋና ትላልቅ ጥቅሞች የሚሰጡ በርካታ ንብረቶችን ከተለያዩ መንግሥታዊና ወታደራዊ ተቋሞች፤ ዩኒቨርስቲዎች፤ ሆስፒታሎች፤ ማህበራዊና ኤኮኖሚያዊ አገልግሎት መስጫዎች ዘርፎ እስከዛሬ ትክክለኛ አደራሻው ለሕዝብ ይፋ ወደ አልተደረገ የሰሜን አካባቢ አይናችን እያየ በረጃጅም የጭነት መኪናዎች አጓጉዞአል። በቀድሞ መንግሥት ዘመን ምንም ዕጥረት እንዳልነበረው የሚታወቀውን የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትና የ24 ሰዓት መብራት አገልግሎትን እንኳ ሳይቀር በማስተጓጎል የከተማውን ሕዝብ ተበቅሎአል።
ወያኔ አዲስ አበባ ከተማ ላይ ያለውን ጥላቻ በጥቂቱም ቢሆን ረገብ ያደረገ የሚያስመስል እንቅስቃሴዎችን ማድረግ የጀመረው በሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች ነው። አንደኛው ምክንያት በቃኝ የማያውቁት የቀድሞ ተጋዳላዮች የአገሪቱን አንጡራ ሃብት እንዲበዘብዙ በተመቻቸላቸው እድል ዘርፈው የያዙትን ገንዘብ ከውልደታቸው ጀምሮ ከሚታወቁበት አካባቢ ሕዝብ እይታ አርቀው “ለደም ካሳ” በዋና ከተማችን እምብርት በነፃ በታደላቸው የከተማ ቦታዎች ላይ ህንጻዎችን በመገንባት ንብረት እንዲይዙ ሁኔታዎችን ለማመቻቸት ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ በርካታ የአለም አቀፍ ድርጅቶችና ዲፕሎማቶች መቀመጫ በሆነቺው አዲስ አበባ ምርጫ 97ን ተከትሎ ገጥሞት የነበረው ሽንፈት ባስከተለው መዘዝ የተበላሸ ገጽታውን በህንጻና መንገዶች ግንባታ ስም ለማሳመር መጣር ናቸው።
የአዲስ አበባ ኮንደሚኒዬም ቤቶቾ ግንባታ ከምርጫ 97 ቦኋላ በመኖሪያ ቤቶች እጥረት የሚሰቃየውን ሕዝብ ልብ ለማማለልና የፖለቲካ ድጋፍ ለመግዛት ያስችላል ተብሎ የታሰበ ብቻ ሳይሆን የሚከተሉት ድብቅ ዓላማዎችም አሉት።
  1. በዘረፋ የከበሩ የቀድሞ ተጋዳላዮችና የጥቅም ተካፋዮቻቸው አይናቸው ያረፈባቸውን ቁልፍ የመኖሪያና የንግድ ቦታዎች ሁሉ ለዘመናት በባለይዞታነት ይዘው የኖሩትን በልማትና በእንቨስትመንት ሥም በማፈናቀል ወደ ግላቸው ላማዞር ያስችላቸዋል፤
  2. በተለያዩ ሥም የተቋቋሙ የህንጻ ሥራ ተቋራጭ ድርጅቶቻቸው በግንባታው ሥራ በመሳተፍ መጠነ ሰፊ የሆነ ትርፍ ለማግበስበስ ያመቻቸዋል፤
  3. የሥርዓቱን ደጋፊዎችና አቀንቃኞች ከሌላ ቦታ አምጥቶ በማስፈር በጠላትነት የተፈረጀውን የኅብረተሰብ ክፍል ተጽዕኖ ለማምከን ይረዳል፤
  4. በሀብት ዘረፋው ለመሳተፍ እድል የሌላቸው የበታች ካድሬዎችና ታማኝ አገልጋዮችን ተጠቃሚ በማድረግ በአለቆቻቸው ዘረፋ ተማረው ልባቸው እንዳይሸፍት ይከላከላል ፤
  5. ከተወለዱበትና ካደጉበት የግልና የቀበሌ ቤቶች ያለውደታቸው የተፈናቀሉ ዜጎች የኮኖዶሚኒየሙን ሂሳብ መክፈል እስከቻሉ ድረስ “ከቤታችን ተፈናቅለን ሜዳ ላይ ተጣልን” የሚል እሮሮ በማሰማት መንግስት ላይ አመጽ እንዳያስነሱ ስጋት ለመቀነስ ይረዳል፤
  6. ከሰሞኑ 40 ከመቶ ተብሎ በወጣው ፖሊሲ እንደታዘብነው ደግሞ ዜጎችን በማጓጓት ተቸግረው ያጠራቀሙትን ገንዘብ ዝግ የባንክ ሂሳብ ውስጥ እንዲከቱ በማድረግ የገንዘብ እጥረት አንገቱ ድረስ የዘለቀውን አገዛዝ ለመታደግ ያስችላል (በ16 የሥራ ቀናት ብቻ ከተመዘገበው 750, 000 የኮንዶሚንዬም ቤት አመልካች 750 000 000 (ሰባት መቶ ሃምሳ ሚሊዮን) ብር መሰብሰቡን ልብ ይሏል)
ከዚህም በተጨማሪ የኮንደሚኒዬም ቤቶች ግንባታ በቂ ጥናትና ዝግጅት ያልተደረገበት የይድረስ ይድረስ ሥራ መሆኑን የቤቶቹ ርክክብ በተፈጸመ ማግሥት ስለ ህንጻው መሬት ውስጥ መስጠምና መጣመም መጀመር እየወጥ ያሉ ዜገባዎች ዋቤ ምስክር ናቸው።
የወያኔ መሪዎችና ታማኝ አገልጋዮቻቸው ከኮንደሚኒዬም ግንባታ በተጨማሪ ከምርጫ 97 ወዲህ ከፍተኛ ገንዘብ እያግበሰበሱ ያሉት የከተማ ቦታዎችን በውድ ዋጋ የልጅ ልጆቻቸው እንኳ ሊደርሱበት ለማይችል የግዜ ገደብ በሊዝ በመቸብቸብ ነው። በዚህ የመሬት ቅሪሚያ አንዳንድ ስግብግቦች “የአባትህ ቤት ሲዘረፍ አብረህ ዝረፍ” እንዲሉ “ወያኔዎች መሬታችንን እየተቀራመቱ ስለሆነ ተሻምተን ማስቆም አለብን” በሚል ብልጣ ብልጥነት ከሚኖሩበት የስደት አገር እየተጓዙ የወያኔን ገቢያ በማድራት ላይ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ሕዝብ በትዝብት ተመልክቶአል። አገርን ዘርፎ ለዘራፊ እየሰጠ ያለ መንግሥት ሴራ ተባባሪ መሆን በሞራልም ሆነ በህሊና ዳኝነት የሚያስጠይቅ ወንጀል መሆኑ ሳያንስ እነዚህ በስግብግብነት የተጠመዱ ወገኖች ለንብረታቸው ደህንነት ሲባል ወያኔ ዓይናቸው እያየ ጆሮአቸው እየሰማ በሌሎች ወገኖቻቸው ላይ የሚፈጽማቸውን ሰቆቃዎች እንኳ ለመቃወም ድፍረት በማጣት ሌላ ትዝብት ውስጥ ሲወድቁ ተስተውለዋል:: ለመሆኑ እነዚህ ወገኖች ለፍተው ባገኙት ገንዘብ የገዙት ባርነትን ነው ወይስ የንብረት ባለቤትነትን ለሚለው ጥያቄ ምላሽ ይኖራቸዋል?
የዜጎች መብት በተከበረበት አገር ከዜግነት መብቶች አንዱ የግል ሀብት ባለቤት ለመሆን ገደብ የሌለው ነፃነትና እድል መኖሩ ነው:: ወያኔ በሚያስተዳድራት ኢትዮጵያችን ግን የንብረት ባለቤት ለመሆን የሥርዓቱ ባለሟል መሆን አለያም ከፖለቲካ ባላንጣነት መራቅ ዋና መስፈርት ናቸው። በዚህ መስፈርት ከወያኔ ጋር ተሻምተው ወይም ተሻርከው የንብረት ባለቤት ለመሆን እየተሽቀዳደሙ ያሉ ወገኖች ሊያውቁት የሚገባው ሃቅ ቢኖር አድሎአዊነት በሰፈነበት መንገድ የተገኘ ማንኛውም አይነት ሀብት ወይም ንብረት ወደፊት በወያኔ ከርሰ መቃብር ላይ በሚመሰረተው ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ ህገዊ ጥበቃ የሚኖረው አለመሆኑን ነው። ብሄራው የአገር ጥቅም ላይ ክህደት ከፈጸመ ፤ ዜጎችን በማፈን ሰቆቃ ካደረሰ ፤ የአገሪቷን ዜጎች ከቤት ንብረታቸው በማፈናቀል መሬታቸውን ቀምቶ ለሌሎች አሳልፎ ከሰጠ ፤ የመንግሥትና የሕዝብ ሀብት ዘርፎ ለዘራፍ ከሰጠ ወንጀለኛ መንግሥት ጉያ ውስጥ ተወሽቆ እስከ ወዲያኛው የህግ ጥበቃ ሊደረግለት የሚችል ንብረት ባለቤት መሆን ማሰብ እጅግ ይቸግራል። ዜጎች በራሳቸው ወዝ ለፍተው ያገኙትን ንብረት ሳይቀር በፖለቲካ አስተሳሰባቸው ምክንያት ብቻ በሽብርተኝነት እየፈርጀ የሚነጥቅ ሥርዓት ዕድሜ እንደምንጠብቀው ረዥም ሊሆን እንደማይችል ማሰብ ብልህነት ነው።
ግንቦት 7 የፍትህ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ የወያኔ አገዛዝ በውጭው ዓለም በስደት ከሚኖረው ወገናችን በአባይ ግድብ የቦንድ ሺያጭ ሥም ለመሰብሰብ ሞክሮ ያልተሳካለትን ገንዘብ በመሬት ሺያጭ እና በኮንደሚኒዬም ቤት ግዥ ሥም እንዲያገኝ ሊፈቀድለት አይገባም ብሎ ያምናል:: ስለዚህም እያንዳንዱ ነፃነት ናፋቂ ኢትዮጵያዊ ከዚህ ከኮንደሚኒዬም ቤቶች በስተጀርባ ያለውን ድብቅ አጀንዳ በማጋለጥ ጥረቱን በማምከን የሕዝባዊ እምብተኝነት ትግል አካል እንዲሆን ግንቦት 7 የትግል ጥሪውን ያስተላልፋል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ

EU delegation: Ethiopia should release jailed journalists and activists

ADDIS ABABA, Ethiopia — A European Union parliament delegation on Wednesday called on Ethiopia’s government to release jailed journalists and activists, but in a sign the call may not be heeded the delegation was denied from visiting a prison it had been approved to see.

The head of the delegation, Barbara Lochbihler, said Ethiopia is jailing journalists and activists for “exercising their legitimate right to freedoms of expression, association and religion.” The group is concerned by reports of misuse of the country’s anti-terrorism legislation to stifle dissent, she said.
“Despite the country’s excellent constitution, we note flaws in the impartiality of the judicial system,” Lochbihler told journalists at a press conference Wednesday.
A spokesman for the Ethiopian Prime Minister said the country doesn’t have any political prisoners and that prisoners would not be released “just because some European Union members said so.”
According to the Committee to Protect Journalists, the Ethiopian government criminalizes the coverage of any group the government deems to be a terrorist group, a list that includes opposition political parties.
“Among those jailed is Eskinder Nega, an award-winning blogger whose critical commentary on the government’s extensive use of anti-terror laws led to his own conviction on terrorism charges,” the group said in its latest survey, which placed Ethiopia among the world’s top ten worst jailers of journalists.
The EU parliament delegation said certain broadcasters are jammed in Ethiopia and that access to the Internet and social media are “regularly restricted.” The practice is at odds with the Ethiopian constitution, the delegation said in a statement.
The four-person delegation, drawn from the parliament’s subcommittee on human rights, said the Ethiopian government must guarantee freedom of speech and the right to peaceful assembly at all times in accordance with its constitution and obligations under international law. The delegation met top government officials, activists and leaders of the opposition.
Earlier on Wednesday the delegation was scheduled to visit to the country’s Kaliti prison where most activists are believed to be serving their sentence. But the prison director turned the group back on arrival, saying “he didn’t have time to work with you,” according to a member of the delegation, Jorg Leichtfried.
Leichtfried told a news conference their visit was “overshadowed” by the incident. He described it as an episode he doesn’t wish to experience again. All four delegation members spoke about the incident, which appeared to have frustrated them.
The delegation said Ethiopia itself has requested international assistance to improve its detention centers and their visit was to have a firsthand experience of the detention conditions.
Getachew Reda, a spokesman for Ethiopian Prime Minister Hailemariam Desalegn, said he was not aware of any decisions either to grant permission to see the prison or to deny it. Getachew said only family members can visit the prisoners.
“We don’t have any single political prisoner in the country. We do have, like any other country, people who were convicted of crimes including terrorism who are currently serving their sentence. They would only be freed when either they complete their sentence or probation on good behavior,” Getachew told the Associated Press on Wednesday. “We are not going to do release anyone just because some European Union members said so.”
He criticized the delegation’s statement, calling it “unhelpful” to relations between Ethiopia and the EU.
The EU is one of Ethiopia’s largest donors with millions of dollar spent on development projects across the country.
Hailemariam was scheduled to meet the visiting delegation on Wednesday night.
The European lawmakers also met with African Union officials. Lochbihler criticized Nigeria and the AU for allowing Sudanese President Omar al-Bashir to travel to Abuja earlier this week. The International Criminal Court has an arrest warrant out for Bashir.
Copyright 2013 The Associated Press. All rights reserved. This material may not be published, broadcast, rewritten or redistributed.

አዜብ መስፍን ከአቶ ገ/ዋህድ፣ አቶ ነጋና ምህረተአብ ጋር በመመሳጠር በ3 መርከብ ስሚንቶ አስጭነው በማስገባት የሙስና ወንጀል መፈፀማቸውን ምንጮች አጋለጡ (ከኢየሩሳሌም አርአያ)

(ከኢየሩሳሌም አርአያ)
ወ/ሮ አዜብ መስፍን ከአቶ ገ/ዋህድ፣ አቶ ነጋና ምህረተአብ ጋር በመመሳጠር በሶስት መርከብ ስሚንቶ አስጭነው
አገር ውስጥ በማስገባት ከፍተኛ የሙስና ወንጀል መፈፀማቸውን ምንጮች አጋለጡ። በተከለከለ ፍራንኮ ቫሉታ ፈቃድ
አገር ቤት የገባው ስሚንቶ በመቶ ሚሊዮን የሚቆጠር ትርፍ አዜብና ግብረአበሮቻቸው እንደዛቁበት ያረጋገጡት
ምንጮቹ፣ አያይዘውም ጉዳዩ በደህንነት ሹም አቶ ጌታቸው አሰፋ እጅ እንደገባ አስታውቀዋል። በሕገወጥ መንገድ
የውጭ ምንዛሪ በከፍተኛ ደረጃ በመመደብና አስፈላጊውን ትእዛዝ በመስጠት እንዲሁም የጥቅም ተካፋይ በመሆን
ግንባር ቀደም ሚና የተጫወቱት አዜብ መስፍን ከዚህ ድርጊታቸው በተጨማሪ ከዚህ ቀደም ከስሚንቶው ጋር በተያያዘ
ተመስርቶ የነበረውን ክስ እንዲቋረጥ ማድረጋቸውን የጠቆሙት ምንጮች፣ ይህና ሌሎች ተያያዥ የወንጀል
ድርጊቶችን የሚያስረዱ ማስረጃዎች በአቶ ጌታቸው እጅ እንደገቡ አረጋግጠዋል። አቶ ነጋ ገ/እግዚያብሄር
በኮንትሮባንድ ቀረጥ ሳይከፈልባቸው ወደ አገር ውስጥ ያስገቧቸው የህክምና መሳሪያዎች ተይዘው ክስ
ከተመሰረተባቸው በኋላ ክሱ እንዲቋረጥ ያደረጉት አዜብ መሆናቸውን የገለፁት ምንጮቹ፣ በተለያዩ ጊዜያት የገቡና
የነጋ ገ/እግዚያብሄር ንብረት የሆኑ ከባድ ተሽከርካሪዎች ያለቀረጥ እንዲገቡ በማድረግ አዜብ መተባበራቸውን
አያይዘው ገልፀዋል። ጉዳዩም «ክስ በማቋረጥ..» በሚል በሰነድ ተደግፎና ከሌሎች መሰል ድርጊቶች ጋር ተያይዞ
በታሳሪዎች ላይ ክስ የቀረበ ቢሆንም፣ ዋናው ተዋናይ ግን አዜብ ሳይጠየቁ መቅረታቸው አነጋጋሪ መሆኑን ምንጮቹ
አልሸሸጉም። ከስሚንቶው ጋር በተያያዘ አስተያየት
የጠየኳቸው ታዋቂ የሆኑ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ባለሙያ ፥ «
መንግስት ስለ ፍራንኮ ቫሉታ ሕግ አውጥቷል፤ ይህን
በመተላለፍ ሶስት መርከብ ስሚንቶን የሚያክል ነገር
በታሳሪዎቹ ብቻ ሊፈፀም አይችልም፤ ከዚህ ሕገወጥ ድርጊት
በስተጀርባ ትልቅና ቁልፍ ስልጣን ያለው ሰው እጁ
እንዳለበት ግልፅ ነው።» ብለዋል።
በተያያዘም ስለ ነጋ ገ/እግዚያብሄርና ገ/ዋህድ ወ/ጊዮርጊስ
የጀርባ ታሪክ በተመለከተ ምንጮቹ ተከታዩን መረጃ
አስቀምጠዋል፤ “ ሕወሐት/ኢህአዴግ ወደ ስልጣን ሲመጣ
የአቶ ነጋ ስራ የመኪና ድለላና ኮረዶችን ከባለስልጣናት ጋር
የማገናኘት የድለላ ተግባር ላይ ተሰማርቶ እንደነበረ
ይገልፃሉ። በተለይ ሴቶችን እየመረጠ ለበርካታ የገዢው
ሹማምንት ለወሲብ ከማቅረብ ጎን ለጎን የሕወሐት ቁልፍ
ባለስልጣናትን በእጁ የማስገባት አጋጣሚ ፈጥሮለታል ፥
ይላሉ ምንጮቹ። ከባዶ ተነስቶ ሚሊየነር የሆነበት ምስጢሩ
አዜብ መስፍን መሆናቸውን ያሰምሩበታል። ለዚህም «ነፃ
ትሬዲንግ፣ ባሰፋና…» ሌሎች ከፍተኛ የቢዝነስ ተቋማቱና በሕገወጥ የዘረፋ ተግባር በድፍረት ተሰማርቶ መቆየቱን
ከሞላ ጎደል ይጠቅሳሉ። በባለስልጣናቱ ተረማምዶ ከአዜብ ጋር በፈጠረው <ልዩ ቁርኝት> የተገኘ ሃብት እንደሆነ
ይገልፃሉ። ከአዜብ ጋር በማሌዢያና ለንደን የፈፀሟቸው አስነዋሪ ተግባራት የሚያሳዩ የምስል ማስረጃዎች በደህንነት
ሃላፊው እጅ እንደገቡ የጠቆሙት ምንጮቹ፣ የሁለቱን ግንኙነት በተመለከተ አብዛኛው የሕወሐት አመራር ጠንቅቆ
እንደሚያውቀው አስታውቀዋል። አቶ ነጋ በቁጥጥር ስር ሲውሉ ማመን ተስኗቸው ከማንገራገራቸው ባሻገር፥
«..ለአዜብ ስልክ እንድደውል ፍቀዱልኝ?» በማለት መማፀናቸውንና ደህንነቶቹ እንዳልተቀበሏቸው ምንጮቹ
አመልክተዋል። በሌላም በኩል ከአዜብ ጋር ተመሳሳይ <ግንኙነት> ያላቸው ሌሎች ሁለት ባለሃብቶች፥ አንዱ 40
ሚሊዮን የፈጀ ባለስድስት ፎቅ የቢዝነስ ተቋም (ቦሌ ከሜጋ አጠገብ) አዜብ በለገሱት ገንዘብ እንዲገነባ ሲደረግ፣ ከዚህ
ግለሰብ ጋር በተደጋጋሚ በዱባይ በውቂያኖስ ላይ በተገነባውና የቱጃሩ አልወሊድ ቢንጣለል ንብረት በሆነው
“ኪንግደም” ባለ4 ኮከብ እጅግ ዘመናዊ ሆቴል እንደተገናኙ፣ እንዲሁም ሌላኛው የአንድ ቢሊየን ብር ባለሃብት ሆኖ
ከፍተኛ ደረጃ እንዲደርስ አዜብ ማድረጋቸውን ምንጮቹ አጋልጠዋል።
የአቶ ገ/ዋህድ ማንነት በተመለከተ ምንጮቹ ይህን ይላሉ፤ « ገ/ዋህድ የኢሰፓ አባል ሆኖ በአስመራ እስከ 1982ዓ.ም
ያገለግል ነበር። በዚሁ አመት መጨረሻ በራማ በኩል አድርጎ ሕወሐትን ተቀላቀለ። በወቅቱ በመቀሌ እንዲቋቋም
በተደረገውና የቀድሞ የደርግ ከፍተኛ መኮንኖች (ምርኮኛ) የተካተቱበት <ኢዴመአን> የተባለ ድርጅት መስራች አባል
ነበር – ገ/ዋህድ። በ1983 ዓ.ም የሁለት ሳምንት ወታደራዊ ስልጠና ወይም በድርጅቱ አጠራር “ተአለም” ከወሰደ
በኋላ በአጋጣሚ ፓርቲው መላ አገሪቱን እንደተቆጣጠረ ምንጮቹ ያመለክታሉ። በሲቪል ሰርቪስ አልፎ ደቡብን
ከጀርባ እንዲመሩ ከተመደቡት አቶ ቢተው በላይ ጋር በአዋሳ ተመደበ። በ1993ዓ.ም በተፈጠረው የፓርቲው
መሰንጠቅ አመቺ አጋጣሚ የተፈጠረለት ገ/ዋህድ የክልሉን ፕ/ት አቶ አባተ ኪሾን፣ ቢተው በላይና ሌሎችም
እንዲታሰሩ በማድረግ ከፍተኛ ሚና ተጫወተ። ለዚህ ታማኝነቱ የላቀ ቦታ በመለስ ማግኘት እንደቻለና ከዛ በኋላ
በየቀኑ ከአዜብና መለስ ጋር በስልክ ይገናኝ እንደነበረ በፈለገው ጊዜ ቤተመንግስት ይገባና ይወጣ እንደነበረ ምንጮቹ
አረጋግጠዋል። በአዜብ መልካም ፈቃድ በጉምሩክ ወሳኝ ስልጣን እንዲጨብጥ መደረጉንም አክለው ገልፀዋል።
ከአዜብና ሸሪኮቻቸው ጋር በመነጋገርና በመመሳጠር ስሚንቶና ሌሎች ቁሳቁሶች በህገወጥ መንገድ ቀረጥ
ሳይከፈልባቸው አገር ቤት እንዲገቡ በማድረግ ከፍተኛ ሚና የተጫወተው ገ/ዋህድ፣ በሚሊዮን የሚገመት ሃብት
ከዘረፋው እንዳተረፈም ተመልክቷል። ባለቤቱ ኮ/ል ሃይማኖትም እንዲሁ አዜብ በሚመሩት የሴቶችና ፀረ-ኤድስ
ተቋም በምክትል ሃላፊነት እንዲመደቡና በየአመቱ ከአሜሪካ ብቻ እስከ 240 ሚሊዮን ዶላር በእርዳታ መልክ
የሚገኘውን ገንዘብ በግልፅ በመዝረፍ ተባባሪ ሆነው መቆየታቸውን ምንጮቹ አስታውቀዋል።

fredag 19. juli 2013

ከፍተኛ የሙስና ወንጀል ሲጋለጥ (ከኢየሩሳሌም አርአያ)

  • ከፍተኛ የሙስና ወንጀል ሲጋለጥ
    (ከኢየሩሳሌም አርአያ)
    ወ/ሮ አዜብ መስፍን ከአቶ ገ/ዋህድ፣ አቶ ነጋና ምህረተአብ ጋር በመመሳጠር በሶስት መርከብ ስሚንቶ አስጭነው አገር ውስጥ በማስገባት ከፍተኛ የሙስና ወንጀል መፈፀማቸውን ምንጮች አጋለጡ። በተከለከለ ፍራንኮ ቫሉታ ፈቃድ አገር ቤት የገባው ስሚንቶ በመቶ ሚሊዮን የሚቆጠር ትርፍ አዜብና ግብረአበሮቻቸው እንደዛቁበት ያረጋገጡት ምንጮቹ፣ አያይዘውም ጉዳዩ በደህንነት ሹም አቶ ጌታቸው አሰፋ እጅ እንደገባ አስታውቀዋል። በሕገወጥ መንገድ የውጭ ምንዛሪ በከፍተኛ ደረጃ በመመደብና አስፈላጊውን ትእዛዝ በመስጠት እንዲሁም የጥቅም ተካፋይ በመሆን ግንባር ቀደም ሚና የተጫወቱት አዜብ መስፍን ከዚህ ድርጊታቸው በተጨማሪ ከዚህ ቀደም ከስሚንቶው ጋር በተያያዘ ተመስርቶ የነበረውን ክስ እንዲቋረጥ ማድረጋቸውን የጠቆሙት ምንጮች፣ ይህና ሌሎች ተያያዥ የወንጀል ድርጊቶችን የሚያስረዱ ማስረጃዎች በአቶ ጌታቸው እጅ እንደገቡ አረጋግጠዋል። አቶ ነጋ ገ/እግዚያብሄር በኮንትሮባንድ ቀረጥ ሳይከፈልባቸው ወደ አገር ውስጥ ያስገቧቸው የህክምና መሳሪያዎች ተይዘው ክስ ከተመሰረተባቸው በኋላ ክሱ እንዲቋረጥ ያደረጉት አዜብ መሆናቸውን የገለፁት ምንጮቹ፣ በተለያዩ ጊዜያት የገቡና የነጋ ገ/እግዚያብሄር ንብረት የሆኑ ከባድ ተሽከርካሪዎች ያለቀረጥ እንዲገቡ በማድረግ አዜብ መተባበራቸውን አያይዘው ገልፀዋል። ጉዳዩም «ክስ በማቋረጥ..» በሚል በሰነድ ተደግፎና ከሌሎች መሰል ድርጊቶች ጋር ተያይዞ በታሳሪዎች ላይ ክስ የቀረበ ቢሆንም፣ ዋናው ተዋናይ ግን አዜብ ሳይጠየቁ መቅረታቸው አነጋጋሪ መሆኑን ምንጮቹ አልሸሸጉም። ከስሚንቶው ጋር በተያያዘ አስተያየት የጠየኳቸው ታዋቂ የሆኑ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ባለሙያ ፥ « መንግስት ስለ ፍራንኮ ቫሉታ ሕግ አውጥቷል፤ ይህን በመተላለፍ ሶስት መርከብ ስሚንቶን የሚያክል ነገር በታሳሪዎቹ ብቻ ሊፈፀም አይችልም፤ ከዚህ ሕገወጥ ድርጊት በስተጀርባ ትልቅና ቁልፍ ስልጣን ያለው ሰው እጁ እንዳለበት ግልፅ ነው።» ብለዋል።
    በተያያዘም ስለ ነጋ ገ/እግዚያብሄርና ገ/ዋህድ ወ/ጊዮርጊስ የጀርባ ታሪክ በተመለከተ ምንጮቹ ተከታዩን መረጃ አስቀምጠዋል፤ “ ሕወሐት/ኢህአዴግ ወደ ስልጣን ሲመጣ የአቶ ነጋ ስራ የመኪና ድለላና ኮረዶችን ከባለስልጣናት ጋር የማገናኘት የድለላ ተግባር ላይ ተሰማርቶ እንደነበረ ይገልፃሉ። በተለይ ሴቶችን እየመረጠ ለበርካታ የገዢው ሹማምንት ለወሲብ ከማቅረብ ጎን ለጎን የሕወሐት ቁልፍ ባለስልጣናትን በእጁ የማስገባት አጋጣሚ ፈጥሮለታል ፥ ይላሉ ምንጮቹ። ከባዶ ተነስቶ ሚሊየነር የሆነበት ምስጢሩ አዜብ መስፍን መሆናቸውን ያሰምሩበታል። ለዚህም «ነፃ ትሬዲንግ፣ ባሰፋና…» ሌሎች ከፍተኛ የቢዝነስ ተቋማቱና በሕገወጥ የዘረፋ ተግባር በድፍረት ተሰማርቶ መቆየቱን ከሞላ ጎደል ይጠቅሳሉ። በባለስልጣናቱ ተረማምዶ ከአዜብ ጋር በፈጠረው <ልዩ ቁርኝት> የተገኘ ሃብት እንደሆነ ይገልፃሉ። ከአዜብ ጋር በማሌዢያና ለንደን የፈፀሟቸው አስነዋሪ ተግባራት የሚያሳዩ የምስል ማስረጃዎች በደህንነት ሃላፊው እጅ እንደገቡ የጠቆሙት ምንጮቹ፣ የሁለቱን ግንኙነት በተመለከተ አብዛኛው የሕወሐት አመራር ጠንቅቆ እንደሚያውቀው አስታውቀዋል። አቶ ነጋ በቁጥጥር ስር ሲውሉ ማመን ተስኗቸው ከማንገራገራቸው ባሻገር፥ «..ለአዜብ ስልክ እንድደውል ፍቀዱልኝ?» በማለት መማፀናቸውንና ደህንነቶቹ እንዳልተቀበሏቸው ምንጮቹ አመልክተዋል። በሌላም በኩል ከአዜብ ጋር ተመሳሳይ <ግንኙነት> ያላቸው ሌሎች ሁለት ባለሃብቶች፥ አንዱ 40 ሚሊዮን የፈጀ ባለስድስት ፎቅ የቢዝነስ ተቋም (ቦሌ ከሜጋ አጠገብ) አዜብ በለገሱት ገንዘብ እንዲገነባ ሲደረግ፣ ከዚህ ግለሰብ ጋር በተደጋጋሚ በዱባይ በውቂያኖስ ላይ በተገነባውና የቱጃሩ አልወሊድ ቢንጣለል ንብረት በሆነው “ኪንግደም” ባለ4 ኮከብ እጅግ ዘመናዊ ሆቴል እንደተገናኙ፣ እንዲሁም ሌላኛው የአንድ ቢሊየን ብር ባለሃብት ሆኖ ከፍተኛ ደረጃ እንዲደርስ አዜብ ማድረጋቸውን ምንጮቹ አጋልጠዋል።
    የአቶ ገ/ዋህድ ማንነት በተመለከተ ምንጮቹ ይህን ይላሉ፤ « ገ/ዋህድ የኢሰፓ አባል ሆኖ በአስመራ እስከ 1982ዓ.ም ያገለግል ነበር። በዚሁ አመት መጨረሻ በራማ በኩል አድርጎ ሕወሐትን ተቀላቀለ። በወቅቱ በመቀሌ እንዲቋቋም በተደረገውና የቀድሞ የደርግ ከፍተኛ መኮንኖች (ምርኮኛ) የተካተቱበት <ኢዴመአን> የተባለ ድርጅት መስራች አባል ነበር – ገ/ዋህድ። በ1983 ዓ.ም የሁለት ሳምንት ወታደራዊ ስልጠና ወይም በድርጅቱ አጠራር “ተአለም” ከወሰደ በኋላ በአጋጣሚ ፓርቲው መላ አገሪቱን እንደተቆጣጠረ ምንጮቹ ያመለክታሉ። በሲቪል ሰርቪስ አልፎ ደቡብን ከጀርባ እንዲመሩ ከተመደቡት አቶ ቢተው በላይ ጋር በአዋሳ ተመደበ። በ1993ዓ.ም በተፈጠረው የፓርቲው መሰንጠቅ አመቺ አጋጣሚ የተፈጠረለት ገ/ዋህድ የክልሉን ፕ/ት አቶ አባተ ኪሾን፣ ቢተው በላይና ሌሎችም እንዲታሰሩ በማድረግ ከፍተኛ ሚና ተጫወተ። ለዚህ ታማኝነቱ የላቀ ቦታ በመለስ ማግኘት እንደቻለና ከዛ በኋላ በየቀኑ ከአዜብና መለስ ጋር በስልክ ይገናኝ እንደነበረ በፈለገው ጊዜ ቤተመንግስት ይገባና ይወጣ እንደነበረ ምንጮቹ አረጋግጠዋል። በአዜብ መልካም ፈቃድ በጉምሩክ ወሳኝ ስልጣን እንዲጨብጥ መደረጉንም አክለው ገልፀዋል። ከአዜብና ሸሪኮቻቸው ጋር በመነጋገርና በመመሳጠር ስሚንቶና ሌሎች ቁሳቁሶች በህገወጥ መንገድ ቀረጥ ሳይከፈልባቸው አገር ቤት እንዲገቡ በማድረግ ከፍተኛ ሚና የተጫወተው ገ/ዋህድ፣ በሚሊዮን የሚገመት ሃብት ከዘረፋው እንዳተረፈም ተመልክቷል። ባለቤቱ ኮ/ል ሃይማኖትም እንዲሁ አዜብ በሚመሩት የሴቶችና ፀረ-ኤድስ ተቋም በምክትል ሃላፊነት እንዲመደቡና በየአመቱ ከአሜሪካ ብቻ እስከ 240 ሚሊዮን ዶላር በእርዳታ መልክ የሚገኘውን ገንዘብ በግልፅ በመዝረፍ ተባባሪ ሆነው መቆየታቸውን ምንጮቹ አስታውቀዋል።
    በማንደፍሮ መንግስቱ
https://www.facebook.com/photo.php?v=10200309772608009

tirsdag 25. juni 2013

http://www.dagbladet.no/2013/06/25/nyheter/krig_og_konflikt/utenriks/verdens_verste_land/27872885/

tirsdag 11. juni 2013

http://ethsat.com/video/esat-fundraising-program-oslo-norway-feb-2013/
http://ethsat.com/video/esat-abay-bond-protest-in-norway-april-2013/
http://www.youtube.com/watch?v=uLIK8YcPCks
http://www.bt.no/nyheter/lokalt/--Stopp-tvangsflyttingen-2900588.html

fredag 7. juni 2013

ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ (መንግስት ለሕዝብ ጥያቄዎች ምላሽ እንዲሰጥ አሁንም እንጠይቃለን!)

ሰማያዊ ፓርቲ
ሰማያዊ ፓርቲ የጠራው ታላቅ ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ ግንቦት 25 ቀን 2005 ዓ.ም በርካታ ሕዝብ በተገኘበት ደማቅ ሆኖ ተካሂዷል፡፡ ለዚህ ሰልፍ መሳካት ከፍተኛ ድጋፍና አስተዋፅኦ ላደረጉ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ ማህበራት፣ የመገናኛ ብዙኃንና በሰልፉ ለተሳተፉ ዜጎች እንዲሁም ሰልፉ በሰላም እንዲጠናቀቅ ለረዱ የፀጥታ ኃይሎች ፓርቲያችን ልባዊ ምስጋናውን ያቀርባል፡፡Blue Party Ethiopia
ከዚህ በተቃራኒ ግን ይህንን ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ ተከትሎ የገዥው ፓርቲ ባለስልጣናትና የመንግስት ተወካዮች የተለመደውን ተልካሻ አስተያየቶች ሰጥተዋል፡፡ የገዥው ፓርቲ ተወካይ ሰልፉን አስመልክቶ በሰጡት አስተያየት “የሐይማኖት አክራሪነት አጀንዳው አድርጎ ሲንቀሳቀስ የነበረው ሰማያዊ ፓርቲ ዛሬ በጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ድብቅ አጀንዳው ገሃድ ወጣ” በማለት በሰጡት አስተያየት ፓርቲውን ለማንቋሸሽና ለማራከስ ሞክረዋል፡፡ ይህም ፓርቲውን በእጅጉ ያስቆጣ ነው፡፡ ይህ ዓይነቱ መሰረተ ቢስ ፍረጃ የገዥው ቡድን አባላት ለንግግራቸውና ለሚሰጡት አስተያየት ሚዛን የሌላቸው ከመሆኑ ውጭ በፓርቲው ፕሮግራምም ሆነ እንቅስቃሴ ከአሸባሪነት ጋር የሚያገናኘውን አንዳችም ነገር አልጠቀሱም፡፡ ፓርቲው በሕጋዊ መንገድ ተመዝግቦ እየተንቀሳቀሰ የሚገኝ እና በሕገ መንግስቱ በተሰጠው መብት ተጠቅሞ በሕጋዊ ሥነስርዓት ያደራጀውን ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ በእንዲህ አይነት መንገድ መፈረጅ ሰልፉ ከተጠራበት ዓላማና መንፈስ በእጅጉ የራቀ አስተያየት ሆኖ አግኝቶታል፡፡
ፓርቲው ከዚህ በፊትም በተደጋጋሚ በሰጣቸው መግለጫዎች በእስልምና እምነት ተከታዮች ላይ የሚደረገውን ጣልቃ ገብነት መቃወሙ ይታወሳል፡፡ ይህንኑ ጥያቄ በተቃውሞ ሰልፉ ላይ ወደ አደባባይ ይዞ መውጣቱ ሕገ መንግስታዊ የመብት ጥያቄ መሆኑን ይገነዘባል፡፡ ከባለሥልጣኑ የተሰጠው አስተያየት ግን የእስልምና ሐይማኖት ተከታይ ዜጎች በሰላማዊ መንገድ የተቃውሞ ጥያቄ ማቅረባቸውን ገዥው ፓርቲ በበጎ ጎን አለማየቱንና የመብት ጥያቄ የሚያነሱ ዜጎችን ሁሉ ወደ ሽብርተኝነት ፍረጃ ለመክተት የሚያደርገውን ጥረት የሚያመላክት ሆኖ አግኝተነዋል፡፡ በተጨማሪም ገዥው ፓርቲ የእስልምና እምነት ተከታዮችን ኢትዮጵያውያን ዜጎች እንደሆኑ አድርጎ እንደማያያቸውም ሰማያዊ ፓርቲ ተገንዝቧል፡፡
የመንግስት ተወካይ የሆኑት ባለስልጣን በበኩላቸው በሰጡት አስተያየት በሰላማዊ መንገድ ተጠይቆና ታውቆ መንግስት ራሱ ያመነውና እጅግ ሰላማዊ የሆነ የተቃውሞ ሰልፍ እንዲካሄድ ያደረገን ፓርቲ ውጭ የሚገኙ ኃይሎች ተላላኪ አድርጎ ማቅረብ የአብዬን ወደእምዬ እንደሚባለው መሆኑን እየገለፅን ይልቁንም በሕጋዊ መንገድ ተመዝግቦ የሚንቀሳቀሰውን ፓርቲያችንን መንግስት ከልቡ ሊቀበለው እንዳልቻለ አስገንዝቦናል፡፡ በተጨማሪም ይህ አባባል ሰማያዊ ፓርቲን የማይመጥን፤ ፓርቲውም በተግባር እያሳየ ያለውን ሰላማዊ የፖለቲካ እንቅስቃሴ የሚጥስ በመሆኑ አጥብቀን እናወግዘዋለን፡፡ እኝሁ የመንግስት ባለስልጣን በሰላማዊ ሰልፉ የተላለፉት መልዕክቶች ህገ መንግስቱን የሚንዱ ናቸው በማለት በደፈናው ህዝብን ለማታለል ከመሞከራቸው በተለየ የትኛው ሃሳብ የትኛውን የሕገ መንግስት ድንጋጌ እንደሚፃረር ካለማመልከታቸውም በላይ ፓርቲው በፍርድ ቤት ጉዳይ ጣልቃ እንደገባ አድርጎ ለማሳየት መሞከር የመንግስትን ግብር ለሰማያዊ ፓርቲ መስጠት ከመሆኑም ሌላ ላም ባልዋለበት ኩበት ለቀማ ያደርገዋል፡፡
በመጨረሻም የእስልምና እምነት ተከታይ ዜጎቻችን ማንኛውንም የመብት ጥያቄ ከሌሎች ወገኖቻቸው ጋር በሰላማዊ መንገድ የማቅረብ ሕገ መንግስታዊ መብታቸው መሆኑን መንግስትም ሆነ ገዥው ፓርቲ እንዲያውቀው እያሳሰብን፤ ሰማያዊ ፓርቲ ከመንግስትም ሆነ ከገዥው ፓርቲ በሚሰጥ ማንኛውም ማስፈራሪያ ከጀመረው የሰላማዊ ትግል ጉዞ ፍፁም ወደ ኋላ እንደማይል፤ ይልቁንም የተነሱትን የሕዝብ ጥያቄዎች መንግስት በሦስት ወራት ውስጥ ምላሽ እንዲሰጥ አሁንም በድጋሚ ማሳሰብ እንፈልጋለን፡፡
ግንቦት 29 ቀን 2005 ዓ.ም አዲስ አበባ

tirsdag 4. juni 2013

mandag 3. juni 2013

http://www.youtube.com/watch?v=lEVENLQ04m4&feature=share
Selam Befkadu's photo.

የወያኔ ፋሽስቶች መሠረትና ዕድገት

ክፍል አንድ
በኢትዮጵያ ምድር ለመጀመሪያ ጊዜ ዘርን መሠረት ያደረገ የፖለቲካ ድርጅት በ1942 ዓ.ም ለጣሊያን በባንዳነት አድረው ሲያገለግሉ በነበሩ የትግራይ ጎጠኞች ተመሠረተ። ከ1928 እስከ 1933 ዓ.ም ሀገራችን በፋሽስት ጣሊያን ተወራ በነበረበት ወቅት ኢትዮጵያውያን አርበኞች ደረታቸውን ለጦር እግራቸውን ለጠጠር ሳይሰስቱ እየሰጡ አገራቸውን ለወራሪ አናስደፍርም ብለው በየጋራውና በየሸንተረሩ ተሰማርተው በኋላ ቀር መሣሪያ ጠላትን ሲፋለሙ ፤ለገንዘብ ወይም ለርካሽ ቁሳዊ ጥቅም ሲሉ ለጠላት አድረው ያገራቸውን ምስጢር የሸጡ፣ከጠላት ጐን ተሰልፈው አገራቸውን የወጉና ያደሙ ባንዳዎች “ቀዳማይ ወያኔ” ብለው በዘር ተደራጁ።
“ቀዳማይ ወያኔ” የሌቦችና የዘራፊዎች ስብስብ ስለነበረ፤በቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ትዕዛዝ በልዑል ራስ አበበ አረጋይ አማካኝነት በ1943 ዓ.ም ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ሥር ውሎ ነበር። ይሁን እንጂ በ1966 ዓ.ም የተደረገን የመንግስት ለውጥ ተከትሎ ሌላ ወያኔ በ1968 ዓ.ም በአቶ ስብሃት ነጋ ተፈጠረ። ይህ በአቶ ስብሃት ነጋ የተመሠተው ሀገር በቀል ፋሽስት ማዕከላዊ አቋሙ “አማራ የትግራይ ህዝብ ቀንደኛ ጠላት ነው” የሚል በመሆኑ ከ1968 ዓ.ም ጀምሮ የአማራን ነገድ ለማጥፋት ዕቅድ አውጥቶ ተግባራዊ በማድረግ ላይ ይገኛል።
አቶ ስብሃት በዘረኝነትና በአልኮል የደንዘዘ ኋላቀር ግለሰብ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም በተመለከት ባላው የተሳሰተ የፖለቲካ አቋም ይታወቃል። ለአብነት “ገዛ ተጋሩ” በተሰኘው የዘረኞች ውይይት ክፍል ውስጥ አሰብ ወደብና የአማራ ነገድን በተመለከተ የሚከተለውን ዘረኛ አቋም አንጸባርቋል። “አሰብ የኤርትራ ወደብ ነው። በዚህ ወደብ ላይ የባለቤትነት ጥያቄ የሚያነሱ የደርግ ሥርዓት ናፋቂና ነፍጠኞች ብቻ ናቸው። በትጥቅ ትግሉ ወቅት አማራ መሬት ስንገባ እናድንሃለን እያልነው የአማራ ገበሬ በሙሉ የወጋንም ንቃተ ህሊናው ትንሽ ስለሆነ ነው ብሏል።”
ይህ ከቂምና ከጥላቻ በስተቀር ፍቅርን የማያውቅ የወያኔ ትግሬ በእርጅና ዘመኑ እንኳ ራሱን መግራት ያቃተው በመሆኑ፤ “ስልጣንን ከኦሮቶዶክስና ከአማራ እጅ ነጠቅናት ይህም የትግላችን ውጤት ነው” ማለቱን ሰምተናል። ባለፉት አርባ ዓመታት የትኛው አማራ፤ የትኛው ኦሮቶዶክስ ስልጣን ይዞ ነበር ቢባል ግን መልስ የለውም። የከሃዲው ስብሃት ነጋ አባባል ግን ለአማራ ነገድና ለኦሮቶዶክስ ቤተክርስትያን ያለውን ሥር የሰደደ ጥላቻ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው። መለስ ዜናዊም በህይወት ዘመኑ ለቤተክርስትያኒቷና ለአማራ ነገድ ባለው ጥላቻ መሠረት ቤተክርስትያኒቷን ለማፍረስ የቻለውን ሁሉ አድርጓል። የአማራንም ነገድ ለማጥፋት ብዙ አረመኔያዊ ተግባራትን ፈጽሟል።በእርሱ የአገዛዝ ዘመን 2.4 ሚሊዮን በላይ አማራ ከቁጥሩ ጎድሎ የት እንደገባ ሳይታወቅ ቀርቷል።
ከ2.4 ሚሊዮን በላይ የአማራ ነገድ የት ገባ ተብሎ የተጠየቀው መለስ ዜናዊ ያለምንም ሃፈረትና ታሪክና ሰው ምን ይለኛል ሳይል “በኤድስ አልቋል” ብሎ በድፍረት መልስ ሰጥቷል።ይሄ በጣም አሳፋሪ እና ነውር ነገር ነው። በተለይም አገርን እመራለሁ ብሎ በህዝብ አናት ላይ ከተቀመጠ ሰው አንደበት ሲወጣ። የወያኔ ፋሽስቶች እንዲህ ያለውን አሳፋሪንና ነውር ነገረን ለይተው አያውቁም ማለት አይቻልም። አንድን ነገድ ለይተው “በኤድስ አለቀ” ብለው መናገራቸው በአማራ ነገድ ላይ የፈጸሙትን የዘር ማጥፋት ወንጀል በግልፅ ያረጋግጣል።
በአጠቃላይ የወያኔ ፋሽስቶች ለአማራ ነገድ የሚፈጽመው የዘር ማጥፋትና ወንጀል ከፍተኛ ደረጃ ላይ ተደርሷል።የሩቁን እንኳን ብንተወው ከ2004 ዓ.ም ጀምሮ ተፋፍሞ በቀጠለው አማራን ከቤትና ከንብረቱ በግፍ የማፈናቀል ዘመቻ ከ100 በላይ አማሮች ተገድለዋል። በመቶ ሺህዎች የሚቆጠሩት ደግሞ ጎዳና ላይ ተጥለው በርሃብ ፣በብርድና በበሽታ በመሞት ላይ ይገኛሉ።ይህንን የዘር ማጥፋት ወንጀል ማስቆምና ወንጀለኞቹን ለፍርድ ማቅረብ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ኃላፊነት ቢሆንም ዘራቸው በመጥፋት ላይ ያለው የአማራ ነገድ አባላት ራሳቸውን ለማዳን የወያኔ ፋሽስቶችን ማግለልና ከህብረተሰቡ እንዲነጠሉ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።
የዐማራ ድምፅ

ምከረው ምከረው እምቢ ካለ ሞክረው…

945562_456214187800412_886270627_nእኔ እኮ ሁልጊዜ ግራ የሚገባኝ አቶ ሽመልስ ከማልን በእንዲህ ያለው ጉዳ ላይ ለምን እንደሚያጋፍጧቸው ነው፡፡ እርሳቸውስ ቢሆኑ አሁንስ አበዛችሁት ራሳችሁ ተናገሩ አይሉም እንዴ…!
ውይ የኔ ነገር ቆይማ ነገርን ከስሩ እንዲሉ ለወጋችን ትንሽ መሰረት ብጤ እንጣልላት፡፡
ትላንት ሰማያዊ ፓርቲ ወንድ ሴት እስላም ክርስቲያን ሳትል በደለኛ ሁላ ና አደባባይ ውጣ እና መንግስትን አብረን እንቆጣው ብሎ ጠርቶ አልነበር… ታድያኮ ባማረ እና በደመቀ መልኩ ፍፁም ሰላማዊ ሆኖ ተጠናቋል፡፡ በእውነቱ ይህ ህዝብ ከመሪዎቹ የሚበልጥ አይደለምን…!
ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የማታ ማታ አስቦ አስቦ ሰልፉን የተመለከተ ዘገባ አቅርቧል፡፡ በዘገባው ላይ የሚመለከታቸው አካል ተብለው ማብራሪያ ሊሰጡ የተጋበዙት አቶ ሽመልስ ከማል ናቸው፡፡
መጀመሪያ ላይ አቶ ሽመልስ ሰልፉን አስመልክቶ የሚነግሩን አለ ሲባል የሰልፉ አስተባባሪ እርሳቸው ነበሩ እንዴ… ብዬ ተደንቄ ነበር፡፡ ኢቲቪ ግን ምንም አይደብረውም… የሰልፉን አስተባባሪዎች እና ተሳታፊዎች አንድ ጥያቄ እንኳ ሳጠይቅ ቀጥታ ከመንግስት ወገን ምላሽ እና ማብራሪያ እንዲሰጡ አቶ አቶ ሽሜን የሚጠራቸው…
የሆነ ሆኖ አቶው መጡና “በሰልፉ ላይ ሲንፀባረቁ የነበሩ መልዕክቶች ከህገመንግስቱ ጋር የሚጣረሱ ናቸው” ብለውን እርፍ አሉት፡፡ አቶ ሽመልስ ይሄንን ያሉት ሃይማኖት እና ፖለቲካ መነጣጠል አለባቸው ከሚል መነሻ እንደሆነ ሊያስረዱን ሞክረዋል፡፡ አባባላቸውን ከኢህአዴግኛ ወደ አማርኛ ስንቀይረው፤ የሀይማኖት ሰዎች የፈለገ በደል ቢደርስባቸው ዝም ብለው ዱዓ ያደርጋሉ እንጂ ለመንግስት አቤት አይሉም የሚል ይመስላል፡፡
እኔ የምለዎ አቶ ሽመልስ… ሃይማኖታቸወን ስላራመዱ ሰዎች መታሰር የለባቸውም… ብሎ መጠየቅ ህገ መንግስቱን እንደመናድ ከተቆጠረ፤ እርስዎን በቴሌቪዥን ማቅረብስ ህገመንግስቱን የመደርመስ ያህል ቢቆጠር ምን ይመስልዎታል…!
አሁንስ ይሄ ህገመንግስት አሳዘነኝ ምንድነው ይሄን ያህል በካርቶን ነው እንዴ የተገነባው በሆነው ባልሆነው የሚፈርሰው!
እዝችው ላይ አቶ ሽመልስ፣ ኢቲቪ እና አንዳንድ ስማቸውን ብንጠቅስም ባንጠቅስም ዋጋ የሌላቸው ሰዎች ሰልፉ ላይ ሙስሊሙ ህብረተሰብ ይበዛል አይበዛም እያሉ ጉንጭ አልፋ እና ፌስ  ቡክ አልፋ ንግግር  ሲናገሩ ተደምጧል፡፡ ተነቧልም፡፡ የሚያስቀው እነዚሁ ግለሰቦች ከሰልፉ ቀደም ብለው በሰልፉ ላይ ሙስሊሙ ህብረተሰብ አይሳተፍም እያሉ ሲቀሰቅሱ የነበሩ ናቸው፡፡
በሰማያዊ ፓርቲ ሰልፍ ላይ ሙስሊሙ ህብረተሰብ አዎ በብዛት ተሳትፏል፡፡ እንደኔ እምነት እንደውም ሰልፉ በሰላም ለመጠናቀቁ አንዱን አስተዋፅኦ ያደረገው ሙስሊሙ ህብረተሰብ በብዛት በመሳተፉ ነው፡፡ ምክንያቱም ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ከአመት ላለፈ ጊዜ ሰላማዊ ተቃውሟቸውን ሲያሰሙ ስለነበረ ያንን ልምድ ለሰማያዊ ሰልፈኞች አጋርተዋል የሚል እምነት አለኝ፡፡
እና ሙስሊሙ ህብረተሰብ በብዛት መሳተፉ ጉዳቱ ምንድነው… ሙስሊሙ በደል ስለደረሰበት ስለሀገሩ ግድ ስለሚለው ተሰለፈ፡፡ ሴቷ በደል ስለ ሀገሯ ግድ ስለሚላት ተሰለፈች፡፡ ወጣቱ በደል ስለደረሰበት እና ስለ ሀገሩ ግድ ስለሚለው  ተሰለፈ፡፡ ጋሽ ታዲዮስ ታንቱም በደል ስለደረሰባቸው እና ስለሀገራቸው ግድ ስለሚላቸው ተሰለፉ፡፡ ታድያ ይሄ ምን ይገርማል…
አቶ ሽመልስ ሌላው ያሉን ነገር “ከቤኒሻንጉል የተፈናቀሉ ዜጎች ጉዳይ መንግስት ቀድሞ መልስ ሰጥቶታል” ብለዋል… አይ ጋሽ ሽሜ… እኔ እኮ ሁልጊዜ ርስዎን ለምን እንዲህ እንደሚጋፍጡዎት ነው የሚገርመኝ፡፡ አቶ በረከት ግን አይወዱዎት የምሬን ነው የምልዎ… እንዲህ ሲናገሩ የሰማዎ ሰው ሁሉ እኮ እንደኮሜዲያን እንጂ እንደባለስልጣን አይመለከትዎትም፡፡ አቶ ሽሜ ለማንኛውም ጥያቄው አፋናቃዮቹ ለፍርድ ይቅረቡ ነው፡፡ ይልቅ ከአፈናቃዮቹ ውስጥ ዝርዝርዎ እንዳይኖር ይስጉ…
የጋዜጠኞችን እስር ጉዳይ፣ የፕሬስ አፈናውን እና የኑሮ ውድነቱን አስመልክቶ የተነሱትን ጥያቄዎች፤ ኢቲቪም አቶ ሽሜም ሆን ብለው የረሱት ወይም በአጠቃቀስኩ ያለፉት ይመስለኛል፡፡ ግን እንዲህ በማደባበስ የትም አይደረስም፡፡
ኢህአዴግዬ ብልጥ ከሆነች የተጠየቀችውን በሙሉ ተግባራዊ አድርጋ ተቃዋሚዎቿን አፍ ማዘጋት ነው ያለባት፡፡
ምከረው ምከረው እምቢ ካለ ሞክረው… ነው እንግዲህ፡፡

søndag 2. juni 2013

በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ላይ ወጥታችሁ ድምጻችሁን ላሰማችሁ ውድ የኢትዮጵያ ልጆች ምስጋና እናቀርባለን

ነፃነት በነፃ እንደማይገኝ አውቃችሁ ለሀገራችሁ እና ለህዝባችሁ መስዋእትነት ለመክፈል ለቆረጣችሁና ፍርሀትን ለሰበራችሁ የቁርጥ ቀን የኢትዮጵያ ልጆች በመላው አለም ተበትነን የምንገኝ የኢትዮጵያ ወቅታዊ መወያያ መድረክ (ECADF) ታዳሚዎች አድናቆታችንና ምስጋናችንን እናቀርባለን።
በተጨማሪም ይህንን ህዝባዊ ሰልፍ ለጠራው እና ላስተባበረው የሰማያዊ ፓርቲ፣ አባላቱና ደጋፊዎቹ እንዲሁም የሰማያዊ ፓርቲን ጥሪ ለደገፉና ለተባበሩ የፖለቲካና ሲቪክ ድርጅቶች፣ በማህበራዊ መገናኛ መረቦች ስትቀሰቅሱና ስታስተባብሩ ለነበራችሁ ለውጥ አራማጆች ያለንን አድናቆት ልናስተላልፍ እንወዳለን።ECADF Statment regarding Addis Ababa's demonstration
እንደተለመደው  እኛ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳዮች መወያያ መድረክ (ECADF) የምንሰባሰብ ኢትዮጵያውያን ምንግዜም ከለውጥ አራማጅ ኢትዮጵያውያን ጎን ተሰልፈን የሚጠበቅብንን አስተዋጽኦ ማበርከት እንደምንቀጥል በድጋሜ ቃል-እንገባለን።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!
ሀገራችን ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!
የኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳዮች መወያያ መድረክ
Ethiopian Current Affairs Discussion Forum (ECADF)
posted by Mandefro Mengistu

lørdag 1. juni 2013

በአዳማ ዩኒቨርሲቲ የሲቪል ምህንድስና ተማሪዎች ተቃውሞ አሠሙ

በአዳማ ዩኒቨርሲቲ የሲቪል ምህንድስና ተማሪዎች ተቃውሞ አሠሙ
ለአንድ ዲፓርትመንት ብለን የዩኒቨርሲቲውን ካሌንደር አንቀይርም” የዲፓርትመንቱ ኃላፊዎች በአዳማ ዩኒቨርሲቲ የሲቪል ምህንድስና የ3ኛ ዓመት ተማሪዎች የወጣውን የፈተና ፕሮግራም በመቃወም ረቡዕ ጠዋት በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ሰላማዊ ሰልፍ አደረጉ፡፡ ተማሪዎቹ “መንግሥት በመደበልን ጊዜና በጀት የመማር መብታችን ይከበር” “There is no exam without education” እና የመሣሠሉ መፈክሮችን አሰምተዋል፡፡ “የዘንድሮው ምዝገባ በሦስት ሳምንት ዘግይቶብናል፣ ከተመዘገብንም በኋላ ሁለት ሳምንት ዘግይተን ነው ትምህርት የጀመርነው” በማለት ቅሬታቸውን ያሰሙት ወደ 300 የሚጠጉት የሲቪል ምህንድስና የሦስትኛ ዓመት ተማሪዎች “አራት ሚድ ተፈትነን ከፋሲካ በዓል ስንመለስ አራት ሜጀር ኮርሶችን አንዳንድ ቻፕተር ብቻ የተማርናቸው አሉ፣ አስተማሪዎች በሥነ-ሥርዓቱ ስለማይገቡ አሁን ጊዜው ሲደርስ ለመጨረስ ቅዳሜ ማታ ሳይቀር እየተዋከብን እንማራለን፣ አንድ ላይ የማይወሰዱ ኮርሶችን በአንድ ላይ እንወስዳለን፣ ቤተ-ሙከራ (ላብ) አናውቅም፤ እስከ አርብ ተምረን ሰኞ ፈተና ልንቀመጥ አይገባም” የሚሉና መሰል ጥያቄዎችን አቅርበው የፈተናው ጊዜ ሊራዘምላቸው እንደሚገባ ጠይቀዋል፡፡
“ተሰብሰቡና እናነጋግራችኋለን” ተብለው “ፓርላማ” በተባለው አዳራሽ ውስጥ የተሰበሠቡት ተማሪዎች ከቆይታ በኋላ ሦስት የዲፓርትመንቱ ኃላፊዎች መጥተው ለማነጋገር ሲሞክሩ ብዙ አለመግባባቶች እንደነበሩ በስብሰባ አዳራሹ ተገኝተን ታዝበናል፡፡ የዲፓርትመንቱ ኃላፊ “ችግሩን ለማቅረብ በጣም ዘግይታችኋል” ተመዝግባችሁ ያልጀመራችሁት ኮርስ ካለ ተውት፣ ጀምራችሁ ያልጨረሳችሁት ኮርስ ካለ ጊዜ ፈልገን ትማራላችሁ፣ የዩኒቨርሲቲው ካላንደርና የፈተና ፕሮግራሙ ግን ለአንድ ዲፓርትመንት ተብሎ አይቀየርም በማለታቸው ተማሪዎቹ ቁጣቸውን በጩኸት ገልጸዋል፡፡ “የፈተና ፕሮግራሙ ለአራተኛ ጊዜ ተቀያይሯል፤ ይህ ለምን እንደሆነ አናውቅም” ስምንት ኮርስ እየወሰድን ጊዜው አጥሮብናል” ያሉት ተማሪዎቹ በሌላ ዩኒቨርሲቲ ዋናውን ፈተና ሰኔ 16 ነው የሚጀምሩት፤ እኛ ግን ገና ተምረን ሳንጨርስ አርብ ጨርሳችሁ ቅዳሜ ውጡ ልንባል አይገባም” በማለት ቅሬታቸውን አሰምተዋል፡፡ አንድ ተማሪ ተነስቶ ባደረገው ንግግር “ምዝገባን ያዘገየው ሌላ ሰው፣ የችግሩ ሰለባ የሆንነው እኛ ነን ሁሉንም ችግር ያላጠፋነውን ሁሉ እንዲንሸከም የምታደርጉት ተማሪውን ነው” በማለት ቅሬታውን ገልጿል፡፡
ተማሪው አክሎም “እኛ እናንተ ምን ኃላፊነት እንዳላችሁ አናውቅም፤ ምንም ስትከታተሉ አይተናችሁ አናውቅም፣ ችግሩን አዘግይታችኋል የምትሉት ትክክል አይደለም፣ የሚሰማን አጥተን ነው እንጂ ስንጮህ ነው የቆየነው፤” አሁንም ቢሆን ጊዜው ተራዝሞ ኮርሶቻችንን ጨርሰን የምንፈተንበት መንገድ ይፈለግልን” ያለው ተማሪው “በዚህ ሁኔታ ከተፈተንን ኪሳራው የተማሪው፣ የዩኒቨርሲቲውና ብሎም የሀገሪቱ ነው” ሌላ ተማሪ በበኩሉ “እኔ በሦስት ዓመት ውስጥ እንደ ምህንድስና ተማሪ ማወቅ የሚገባኝን አውቄያለሁ ብዬ አላምንም” ካለ በኋላ በግቢው አስተማሪ ማስተማርም አለማስተማርም መብቱ እንደሆነ፣ አንዳንድ አስተማሪዎች ፈተና 15 ቀን ሲቀረው እየመጡ እንደሚያጣድፉ፣ ዩኒቨርስቲው ይህን እንደማይከታተልና ችግሩ ሰለባ እየሆነ ተማሪው እንደሆነ በአፅንኦት ተናግሯል፡፡ “አሁን ሰኔ ስምንት እንድንወጣ የሚደረገው በበጀት እጥረት ነው፤ እኛ እንደ ማንኛውም ዩኒቨርሲቲ “ኮስት ሼሪንግ” የምንፈርመው ከመስከረም እስከ ሰኔ 30 ነው፡፡ ስንገባም ጥቅምት አምስት ነው ወደ ጊቢ የመጣነው፡፡ ስለዚህ መንግሥት የመደበልን ጊዜና በጀት እስከ ሰኔ 30 የሚያቆየን በመሆኑ ቀስ ብለን ተረጋግተን ልንፈተን ይገባል” ብሏል፡፡
ኮስት ሼሪንግ የፈረሙበት ፎቶ ኮፒ እጃችን ላይ ይገኛል፡፡ “ሌላው ዩኒቨርሲቲ የራሱ አካሄድ አለው፡፡ አዳማም በትምህርት ሚኒስቴር በተሰጠው ካሌንደር ነው የሚሠራው” ያሉት የዲፓርትመንቱ ኃላፊ “አሁን ችግር ያላችሁት የፈተና ፕሮግራሙ ነው፤ እሱ ላይ ተናገሩ እንጂ ጠቅላላ ችግር አታውሩ” በማለት ቁጣ በተቀላቀለው አጽንኦት ተማሪዎቹን ገስፀዋል፡፡ ይሁን እንጂ ተማሪው ኃሀላፊውን ቁጣ ወደ ጐን በመተው “አንድ ኮርስ በሳምንት ብቻ የምንጨርስበት ሁኔታ አለ፤ እኛ ዴቨሎፕ ሳናደርግ ነው የምንፈተነው፤ ዜጋን ለማዳን ከተፈለገ የማይለወጥ ነገር የለም፡፡ በትምህርቱና በፈተናው መሀል ክፍተት ተሰጥቶን እንፈተን” በማለት ጥያቄያቸውን ቀጥለዋል፡፡ “እኔ ተማሪ በነበርኩበት ጊዜ መማር የሚገባኝን ያህል አልተማርኩም፣ አስተማሪም ከሆንኩ በኋላ ለተማሪዎቼ በአግባቡ አስተምሬያለሁ ብዬ አላምንም” በማለት ለተማሪዎች ምላሽ መስጠት የጀመሩት ሌላው ኃላፊ፤ ይህ ከእኔም ስንፍና፣ ከዩኒቨርሲቲውም ችግር አሊያም በሀገሪቱ ካሉት በርካታ ገደቦች ሊሆን ስለሚችል አሁን ባለው ሁኔታ ቶሎ ቶሎ ጨርሳችሁ ተፈተኑ” ማለታቸው ተማሪዎችን የበለጠ አስቆጥቶ ነበር፡፡ በአዳራሹ ውስጥ ጭቅጭቁ እየከረረ በመሄዱ አንድ ተማሪ አንድ የተሻለ የሚለውን ሐሳብ አቀረበ፤ “አንድ ኮርስ አሳይመንት ሠርተናል፤ እሱ ከመቶ ይታይና መፈተኑ ይቅርብን፡፡
ይህም የሚጠበውን ጊዜ ይቆጥባል ከዚያ በተረፈ ቢያንስ አንድ ቅዳሜ ይጨመርልንና ትንሽ ጋፕ ይኑረን” በማለቱ ኃላፊዎቹ እየከበዳቸውም ቢሆን ለመቀበል ተገደዋል፡፡ ተማሪዎቹ እንደሚሉት በዩኒቨርሲቲው ብዙ ችግር እንዳለባቸውና ፕሮፌሰር ማጁንዳ የተባሉ የቢዩልዲንግ አስተማሪ በሰጡት ግሬድ ስላልታመነበት ከአስተዳደር ክፍሉ በተነሳ ጭቅጭቅ አስተማሪው አጠቃላይ የተማሪዎቹን ውጤት ይዞ ወደ ህንድ በመሄዱ ውጤት በጊዜ ሊታወቅ ስላልቻለ ምዝገባው ለሦስት ሳምንት መዘግየቱን ተናግረዋል፡፡ ኃላፊዎቹም ይህን አምነው አስተማሪውን በኢሜልም በስልክም አነጋግረን ሊታረም ባለመቻሉ ከስራው ማሰናበታቸውንና የምዝገባው ጊዜ መዘግየቱን ተናግረዋል፡፡ “እኛ በአግባቡ አልተማርም ያልዘሩብንን ሊያጭዱ ይሞክራሉ፡፡ ይኼ ለዚህች አገር ውድቀት ከፍተኛ ቁልፍ ነው” ያሉት ተማሪዎቹ ትምህርት ሚኒስቴርና የሚመለከተው አካል ዩኒቨርሲቲውን እንዲቆጣጠረውና እንዲፈትሸው አሳስበዋል፡፡ “ችግሩ የእኛ ዲፓርንመንት ብቻ ሳይሆን የሁሉም ነው” ያለችው አንዲት የዲፓርትመንቱ ተማሪ እኛ ከማወቅ ሳይሆን ከመጨረስ አኳያ ነው እየተዋከብን ያለነው፤ መንግስት ችግራችንን ይወቅልን” ስትል ተናግራለች፡፡ አሁን ባለው ሁኔታ ተማሪዎቹ ያለባቸውን ችግር ችለው እንዲፈተኑና በተባለው ጊዜ ግቢውን እንዲለቁ ትዕዛዝ ተሰጥቶ ስብሰባው ቢበተንም ተማሪዎቹ ቅሬታ እንዳለዙ ሲበታተኑ ለመታዘብ ችለናል፡፡


Source: Addisadmassnews.com
posted by Mandefro Mengistu

ግብጽ በዲፕሎማሲያዊ ኢትዮጵያ ላይ ካልጫንኩ በሚሳኤልም፣ በኮማንዶም፣ በጄትም ልታጠቃ አሰበች ዊኪሊክስ

ባፈው ሰሞን ወሬና “ሚስጢር” አሹላኪው ዊኪሊክስ ከአሜሪካው የደህንነት ድርጅት ስትራትፎር ሾልኮ እጄ የገባው የበየነ መረብ መልዕክት መሰረት ግብጽ በዲፕሎማሲያዊ መንገዶች የምፈልገውን በእነ ኢትዮጵያ ላይ ካልጫንኩ በሚሳኤልም፣ በኮማንዶም፣ በጄትም በመጠቀም በሰዓታት ልታጠቃን አንዳሰበች በሊባኖስ የሚኖሩ ዲፕሎማቷን ጠቅሶ ገልጾልናል፡፡ የግብፃውያን ከአባይ ጋር በተያያዘ ዋናው ችግራቸው በማስፈራራት እና ኃይል በመጠቀም የራሳቸው የሚያደርጉት ይመስላቸዋል፡፡ ይህም የሆነው በዋናነት የአባይ ወንዝ መነሻና ብዙውን ውሃ አበርካች የሆነችው ኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ በጦርነት በመኖሯ እና አቅሟን የማጠናከር ጉዞዋ ያልተስተካከለ በመሆኑ ለውስጥ የደህንነት ጉዳዮች ትኩረት መስጠቷ ውሃውን እንዳትጠቀም እንቅፋት መሆኑ ነው፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ ግብጽ ሱዳንን በመዛት ማስበርገግ መቻሏ እና ከካምፕ ዴቪድ ስምምነት በኋላ ከአሜሪካ የሚጎርፍላት ረብጣ ዶላር እና ዘመናዊ የጦር መሣሪያ ልቧ እንዲያብጥ ስላደረገው ነው፡፡ ከላይ እንዳየነው የጦርነት ክዋኔ በዘመናት ይለያያል እንጅ ባህሪው ባለመለወጡ ምንም መሳሪያ ብታከማች ግብጽ በታሪኳ አትዮጵያን አንድም ጦርነት አሸነፍ አታውቅም፡፡  ከዚህ አንጻር ስንመለከተው በዊኪሊክስ በኩል የሾለከው ጦማር ተራ ወሬ ሊባል የሚችል ነው፡፡ ሆኖም ግን ስንገጣጥማቸው ሙሉ ትርጉም የሚሰጡን ክስተቶችን ስላየን ይህን ጦማር ማቅለል ዋጋ ሊያስከፍል ስለሚችል በአንክሮ መመልከት ተገቢ ነው፡፡ ምንአልባት ምንአልባት አንዳች ክፉ ነገር የህዳሴ ግድቡ ላይ ብታደርስ የማያቋርጥ የውሃ ጥማትን ለሚመጣው የግብጽ ትውልድ ትተዋለች፡፡ እጅግ በጣም ውስብስብ በሆነው መካከለኛው ምስራቅ ውስጥ እየኖረች የእስራኤል እና የአረቦች ጉዳይ ባልለየለት ሁኔታ እንዲህ አይነት እስጣ ገባ ውስጥ መግባት የሚበላው ራሷን ግብጽን ነውና፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ ዊኪሊክስ ይፋ ያደረገው መረጃ እንደሚያሳየው ግብጽ ኢትዮጵያን በሽርክ ለማጥቃት ኩርሲ በተባለች ዳርፉር ሱዳን ውስጥ በምትገኝ ቦታ የሚስጢራዊ ወታደራዊ ማዘዣ እያቋቋመች እንደሆነ ይገልጻል፡፡ ይህ ምን ያክል እውነት ነው? ወደፊት የምናየው ጉዳይ ይሆናል፡፡
posted by Mandefro Mengistu

እኛ ያልነው ለፉገራ… (ክንፉ አሰፋ)

ክንፉ አሰፋ
በሰሞኑ ቀልድ ልጀምር። የአፈሪካ ህብረት ድርጅት 50ኛ አመቱን በያዝነው ሳምንት በአዲስ አበባ ሲያከብር በነበረው የሻምፓኝ ስነ-ስርዓት ላይ አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ብቻ ከመሪዎቹ ተነጥለው ያለ ብርጭቆ  ቆመዋል። ለፕሮቶኮል እንዲመሳሰሉ ቢጠየቁ አሻፈረኝ አሉ። የህብረቱ የወቅቱ ሊቀመንበር ስለነበሩ ለይሰሙላ እንኳን ብርጭቆዋን ጨብጡ ቢባሉ አይሆንም፣ ሃይማኖቴ አይፈቅድም አሉ።  በመጨረሻ ግን በረከት ስምዖን በጆሯቸው አንዳች ነገር ነገራቸውና የያዘውን ብርጭቆ ሲሰጣቸው ተቀብለው በደስታ ጨለጡት።
በረከት ለጠ/ሚ ሃይለማርያም ደሳለኝ በጆሯቸው እንዲህ ነበር ያላቸው። “ብርጭቆ ውስጥ ያለው መለስ የጀመረው ወይን ነው።”
አሁን አሁን መቀለጃ እየሆኑ የመጡት ሃይለማርያም ደሳለኝ፤ መለስ የጀመረውን ሁሉ፤ ፉገራም ቢሆን – ያንን ለመጨረስ ነው የተቀመጥኩት ይሉናል። እየደጋገሙ!
***
ብርኖ  በምትባል የቼክ ሪፐብሊክ ትንሽ ከተማ ከነበርኩበት ሆቴል ውሰጥ የተሰቀለ ቲቪ ካለወትሮው የ’ሕዳሴውን’ ግድብ የሚያሳይ ምስል ይዞ ብቅ አለ። የምሽት ዜና ትንተና መሆኑ ነው። በቼክ ቋንቋ ይተላለፍ የነበረው የዜና ትንተና ባይገባኝም ከምስሉ የመልእክቱን ይዘት ለመረዳት አላስቸገርኝም።
ግን ምን አዲስ ነገር ተገኘ?
የቲቪውን ጣቢያ መቀያየር ጀመርኩ። ሲ.ኤን.ኤን፣ ቢ.ቢ.ሲ.፣ አል ጃዚራ…ቪ.ኦ.ኤ.። የኳታሩ አል ጃዚራ ጉዳዩን በስፋት ይዞታል። Death on the Nile (በአባይ ላይ ግድያ) በሚለው አምዱ ምሁራንን እና ባለስልጣናትን እያቀረበ ስለ ‘ሕዳሴው’ ግድብ ያወያያል። በአሜሪካን መንግስት በሽብርተኝነት የተፈረጀው  የግብጹ ሱኒ ‘አል ጋማ አል ኢስላሚያ’ ድርጅት ደግሞ ኢትዮጵያን በጦር ለመውጋት ዝግጁ መሆኑን ባለፈው ረቡዕ አውጇል።
ሂደቱ እንደገና ሌላ ጥያቄ አጫረብኝ።  የግድቡ ወሬም ሆነ ስራ ከተጀመረ ሁለት አመት ሊሞላው ነው። ዓለም አቀፉ ሜዲያና ዘራፍ ማለት የጀመሩት ቡድኖች ዛሬ ያባነናቸው ምስጢር ምንድነው? አመቱን ሙሉ የት ነበሩ? መልሱን የምናውቀው እኛ ባለቤቶቹ ብቻ ነን። በእርግጥ አቶ መለስ የአባይ ካርድን ይዘው ይጫወቱት የነበረውን ጨዋታ ግብጾች ጠንቅቀው ያውቁት ኖሮ የ’ሕዳሴው’ን ሽርጉድ ከቁብ አልቆጠሩትም ነበር።
ከሁሉም ነገር እንግዳ የሚሆነው፣ በየመገናኛ ብዙሃን እየቀረቡ አስተየት የሚሰጡ የፈረንጅ ‘ምሁራን’ ጉዳይ ብቻ ነው። እነዚህ ተመራማሪዎች ስለ አባይ፣ ስለ ኢትዮጵያ ታሪክ፣ ስለ ኢትዮጵያ ፖለቲካ…ወዘተ ሊቅ ሆነው የተሳሳተ ግምታቸውን እያቀረቡ ሌላውንም ግራ ያጋቡታል።  ስለ ግድቡ በአልጃዚራ አስተያየት ትሰጥ የነበረችዋ ኤክስፐርትም ሂደቱን ‘ብቀላ’ እንደሆነ ገልጻዋለች። ሌላውም እንዲሁ ‘የሕዳሴው ግድብ’ ጦርነት እንደሆነ ገልጿል። የአካባቢ ጥበቃ፣ ኤኮሎጂ… ወዘተ ችግር ያስከትላል የሚሉም አሉ።  ሁሉም አስተያየቶች ግን ከኛ ከሃገሬው አመለካከት የራቁና ከመላምት ያለፉ አይደሉም። እውነታው ሌላ ነው። ፉገራ እና ፉከራ!
በደርግ ጊዜ ነው። መንገድ ላይ ቆሞ አላፊ አግዳሚውን ‘የሚቀፍል’ አንድ ወጣት ነበር። በዚህ ሰው የፖለቲካ ‘ፉገራ’ ፈገግ የሚሉም ሳንቲም ጣል ያደርጉለታል።  አነድ ቀን ‘ኢሰፓኮ፣ ባዶ ባኮ! ‘ እያለ ሲቀልድ ካድሬዎች አይን ውስጥ እንደገባ ነቃና ማምለጫ ዘዴ ፈጠረ።  መንጌን ማወደስ። ‘የሰው ጥራቱ፣ እንደ መንግስቱ!…’ እያለ ከተማውን አቀለጠው። ይህ ዘዴው ከተደገሰለት ሞት ቢያስተርፈውም፣  ከእስር ግን አላስመለጠውም። የማታ ማታ በሚሊሽያዎች ተይዞ ታሰረ። እዚያው ሆኖ እነዲህ አለ። ‘እኛ ያልነው ለፉገራ እነሱ ግን ለመግደል ሙከራ።’
የነጻ ትግል ስፖርት የሚሰሩ አትሌቶች ተመልካቾቻቸውን አልፎ አልፎ ‘Be smart. Don’t try this at home’ ሲሉ ይመክራሉ። ‘አስተውሉ! ይህንን ነገር እቤታችሁ አትሞክሩ።’ እንደማለት ነው።  በቦክስ ሪንግ ውስጥ የሚያደረገው መዝለል፣ መውደቅ እና መነሳት ሁሉ ቀድመው ተለማምደው የሰሩት አክሽን መሆኑን ነው የሚናገሩት። እነዚህ አትሌቶች ለመኖር ሲሉ የሚሰሩት ድራማ እንጂ፣ የሚታየው ድብድብ ሁሉ የ’ፉገራ’ መሆኑን ነው በማስታወቂያቸው የሚናገሩት። በግልጽ ባይሉትም። እንዲህ አይነቱ ጨዋታ ጥበብን ስለሚጠይቅ ማየት እንጂ መሞከሩ አደጋ ያመጣል።
አቶ መለስ ‘Be smart. Don’t try this at home.’ ሳይሉ ማለፋቸው ይመስላል እነ ሃይለማርያም ዛሬ ማኖ እየነኩ ያሉት። ‘መለስ የጀመረውን ለመጨረስ ቃል ገብቻለሁ።’ አይደል እያሉን ያሉት?
ባለፈው ማክሰኞ የአባይ ወንዝ አቅጣጫ መቀልበስ ስራ በኢቲቪ የቀጥታ ስርጭት መታየት ሲጀምር ነው ጫጫታው በዓለም አቀፍ ሜዲያ  የተከተለው። እስከዚህች ቀን ድረስ ግን ኢቲቪ ይቀርበው የነበረው ፕሮፓጋንዳ የኢትዮጵያን ሕዝብ ከማሰልቸት ያለፈ የሜዲያ ትኩረት አልሳበም ነበር። ዜጎችን በፕሮፓጋንዳ በማሰልቸት ኢቲቪ በእውነቱ የሂትለሩን ጆሴፍ ጎብልስ ሚና በደንብ ነው የተጫወተው። ጆሴፍ ጎብልስ እንዲህ ብሎ ነበር።  “ውሸትን እየደጋገምክ ተናገር። በመጨረሻ ሕዝቡ እውነት ነው ብሎ ይቀበለዋል።”
የቅልበሳው ትእይንት ማክሰኞ እስከታየበት ቀን ድረስ የ’ሕዳሴው’ ግድብ ተረት-ተረት እንደሆነ ነበር እነ ግብጽ የሚያውቁት ለማለት የሚያሰቸል ክስተት ነው ያየነው። የግበጽና ሱዳን ጩኸት፣ የሌሎች ቡድኖች ማስፈራሪያ ዛቻና የመገናኛ ብዙሃን ሽፋን ማግኘት የጀመረውም ከዚያ በሗላ ነው። “እኛ የመሰለን ፉገራ …።” እንደማለት ነው።
ነብሳቸውን ይማረውና አቶ መለስም በህይወት ቢኖሩ ኖሮ አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝን ጠርተው፡ “እኛ ያልነው ለፉገራ፤ እናንተ ለመገደብ ሙከራ!” ይሏቸው ነበር።
ኢትዮጵያ ከአባይ ወንዝ ከ80 እጅ በላይ ድርሻ አላት። ይህንን ያህል ለአባይ እየገበርን እሰካሁን በአባይ ወንዝ ተጠቃሚ ያለመሆናችን የሚያንገበግብ ጉዳይ ነው። አባይ ተገድቦ ለኢትዮጵያ ጥቅም ላይ ቢውል የማይደሰት ሰው ቢኖር የኢትዮጵያ ጠላት በቻ ነው።
አሁን በተያዘው መልኩ አባይ ተገድቦ ስራ ላይ ይውላል ብሎ የሚያስብ ካለ ግን ልጅ ውይንም ጅል መሆን አለበት።  ’አባይ ይገደባል’ ብለው የሚከራከሩኝ ወዳጆቼ ለሃገራችን እድገት ካላቸው በጎ ምኞት ያለፈ ሌላ እውነታ እንደሌለው ነው ማስረዳቸው።
የ’ሕዳሴው’ ግድብ፤  የቱኒዥያውን ቤን አሊ፣ የግብጹን ሆስኒ ሙባረክ፣ እንዲሁም የሊቢያውን ጋዳፊ የጠራረገው የሰሜን አፍሪካው ህዝባዊ ማእበል የወለደው ሃሳብ ነው። ለችግር ጊዜ ተቀምጦ የነበረ ጆከር ነው የሳቡት። ይህ ደግሞ የወጣቱን አንደበት ከያዘው የኮብል ስቶን ፕሮጀከት ጋር በመታገዝ እነ መለስን ከማዕበሉ ጠብቋቸዋል።
የ ‘ሕዳሴው ግድብ’ ፕሮጀክት በአምስት አመቱ የ’እድገትና ትራንስፎርሜሽን’ እቅድ ውስጥም አልነበረም። እንደ እንጉዳይ ተክል ከመቅጽበት ብቅ ያለ ነገርም አይደለም። ለዘላቂ ሳይሆን ይልቁንም ላጭር ጊዜ እንደሚወሰድ የእድሜ ማራዘሚያ መድሃኒት አይነት ነው።  አቶ መለስ ዜናዊ የግድቡን መሰረት ሲጥሉ 6ሺህ ሜጋ ዋት የማመንጨቱ ጉዳይ ተግባራዊ ሊሆን እንደማይችልም ጠንቅቀው ያውቁታል።
ለዚህም አንደኛው ምክንያት በ1993 (እ.ኤ.አ.) አቶ መለስ ዜናዊ ከግብጹ ሆስኒ ሙባረክ ጋር ያደረጉት  ስምምነት ነው። (የሁለቱን መሪዎች ፊርማ የያዘውን ይህንን ሚስጥራዊ ስምምነት በወቅቱ ለህትመት በማብቃቴ ለማእከላዊ እስር ተዳርጌ ነበር።) በዚህ ሁለትዮሽ ውል በአንቀጽ አምስት ላይ ‘አንዱ ሃገር ሌላውን ሃገር በሚጎዳ መልኩ ውሃውን መጠቀም አይችልም።’  በማለት ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ ያላትን የተፈጥሮ መብት የሚገፍ ሃረግ ተቀምጧል። ይህ ዲፕሎማሲዊ አንቀጽ በህግ ቋንቋ ሲገለጽ ‘ኢትዮጵያ አነዲት ማንኪያ ውሃ ከአባይ ላይ ብትቀዳ፡ የግብጽን ተፋሰስ ሰለሚቀንስ ከዚህ ድርጊት መቆጠብ አለባት።’ እንደማለት ነው። ከኛ አልፎ ግብፅ ምድር ላይ የሚንፏለለውን ውሃ ካይሮ ተጠቀመች አልተጠቀመች እኛ ምን አገባን?
በአለም አቀፍ ህግ፣ ሁለት ሃገሮች ተስማመተው የሚያጸድቁት ሰነድ ደግሞ ሁለቱ ተስማምተው እስካላፈረሱት ድረስ ሀጋዊ ሰነድ ሆኖ ይቆያል።
አቶ በረከት ስምዖን አልጃዚራ ላይ ባለፈው አርብ ቀርበው፤  በቅኝ ግዛት ወቅት የነበረውን ሰነድ ሲያነሱ፤ የራሳቸው ስርዓት በ1993 ያፀደቀውን ኢትዮጵያ በአባይ ላይ ያላትን የተፈጥሮ እና ሀጋዊ መብት አሳልፎ የሰጠውን ውል እንደዋዛ አልፈውታል። ይህ ሰነድ በቅኝ ግዛት ዘመን ከነበሩ ስምምነቶች ሁሉ የከፋና ለክርክር እንኳን የማያመች ነው።
በአባይ ወንዝ 84 በመቶ ድርሻ ያላት ኢትዮጵያን ያላሳተፉ እነዚያን የቅኝ ግዛት ውሎች ሁሉ ውድቅ ለማድረግ የህግም ሆነ የሞራል የበላይነት አለን ብዬ አምናለሁ።  ግና የ1993ቱ ምስጢራዊ ሰነድ እንዴት ነው ሊፈርስ የሚችለው? ይህ ውል ሳይፈርስ እንዴትስ ነው አባይ ሊገደብ የሚችለው? ለዚህ ጥያቄ እነበረከት በእርግጠኝነት መልስ ሊስጡን አይችሉም።
በሁለተኛ ደረጃ ማየት ያለብን አባይ ዓለም አቀፍ ወንዝ መሆኑን ነው። ዓለም አቀፍ ወንዝ ደግሞ በአንድ ሃገር አዋጅ ሳይሆን፤ በዓለም አቀፍ ህግ ነው የሚመራው። የአባይ ወንዝ ለመጠቀም  የላይኛውና የታችኛው ተፋሰስ ሀገሮች ሁሉ ስምምነት ላይ መድረስ እንዳለባቸው ህጉ ያስገድዳል።
በሶስተኛ ደረጃ አባይን ከምር መገደብ ካስፈለገ፤ አባይን መገደቢያ ገንዘብ አይጠፋም። የህወሃቱ ኢፈረት ብቻውን አንድ አይደለም፤ አራት አባይን መገደብ የሚያስችል ገንዘብ አለው። ገዢው ፓርቲ እርግጥ ለኢትዮጵያ እድገት እና ትራንስፎርሜሽን ስኬት ካሰበ በፓርቲው ስም ያከማቸውን ገንዘብ አውጥቶ ለግድቡ ተግባር ማዋል ይችላል። የኢፈርት ህለቀመሳፍርት ገንዘብ ቢያጓጓው እንኳ በአክሲዎን ሽያጭ ገንዝብ መሰብሰብ ይችል ነበር። ለግድቡ ያስፈልጋል የሚሉን 80 ቢሊየን ብር ነው። እስካሁን ከህዝብ በውዴታም ሆነ በግዴታ ተገኘ የተባለው ደግሞ 7 ቢሊየን ብር። 73 ቢሊየኑን ታዲያ ማን ሊሞላው ይሆን? ወይንስ እንዳሁኑ አይነት ያልተጠበቁ ችግሮች ሲገጥሙ ስራውን ለማቆም እንደምክንያት ሊቀርብ?
ከውስጥ ሰዎች እንደምንሰማው ከሆነ ደግሞ እነ መሶበ ሲሚንቶ እንዲሁም  የህወሃት ኮንስትራክሽን ድርጅቶች የግድቡን መሰረት በመጣል ስም ከህዝብ የተሰበሰበውን 7 ቢሊየን እየተቋደሷት ይገኛሉ። በአንድ ወንጭፍ ሁለት ወፍ .. እንዲሉ። 7 ቢሊየን  ቀላል ገንዘብ አይደለም።  በቅጡ ቢያዝ ኢትዮጵያን ጸብ ውስጥ የማይጨምራት እጅግ ብዙ የሚተገበር የልማት ስራ ላይ ሊውል ይችል ነበር። ኢትዮጵያ ሃይል ሊያመነጩ የሚችሉ በርካታ ትናንሽ ወንዞችም አሏት።
የ’ሕዳሴው ግድብ’ በዚህ ሂደት ተግባራዊ ይሆናል ወይ?  የሚለውን ጥያቄ ምላሽ በቅርብ የምናየው ይሆናል።  ለገዢው ፓርቲ ግዜ መግዣነት ስለማገልገሉ ግን ቅጥ ያጣው የፕሮፓጋንዳ ስራ ብቻ ምስክር ነው። ጫወታው ሳይገባቸው በሃገር ፍቅር ስሜት ብቻ የተሸውዱ እንዳሉ ሁሉ ሕዝቡን ባልተጨበጠ ነገር የሚያሞኙት ልማታዊ ጋዜጠኞች እና ልማታዊ አርቲስቶች ነገ ትዝብት ውስጥ ሊገቡ እንደሚችሉ መገንዘብ ይኖርባቸዋል።
በአንድ ጽሁፌ ለመዳሰስ እንደሞከርኩት በኡጋንዳ – ጂንጃ የነጭ አባይ ምንጭ የሆነው የቡጃጋሊ ግድብ ስራ ተጠናቋል። ኡጋንዳ የነጭ አባይ ምንጭ ነች። ፕሬዚዳንት ሙሴቬኒ  የሃገሪቱን የሃይል አቅርቦት ችግር ለማቃለል የሚያስችል የነጭ አባይ ፕሮጀክት ዘርግተው ተግባራዊም አድርገዋል። ለዚያውም በአለም ባንክ እና በአውሮፓ ህብረት የገንዘብ እርዳታ! ነጭ አባይ የሃገሪቱን የሃይል ምንጭ ችግር ይቀርፋል ተብሎ ይገመታል።
ይህ ግድብ ሲታቀድም ሆነ ሲሰራ ታዲያ በጩኸት እና በመፈክር አልነበረም። የሃገሪቱ አርቲስቶች አልዘፈኑለትም። ሕዝቡ ስለፕሮጀክቱ እንዲጮህለትም ሆነ እንዲጮህበት አልተደረገም። እነደ”ህዳሴ”ው መዋጮ ሁሉ የዜጎች ኪስ አልተበረበረም፤ ከወር ደመወዙ የተቆረጠ ነገር የለም። ቡጋጃሊ ሲገደብ ቦንድ አልተሸጠም፤ ወታደራዊ ማርሽም አልተሰማም።  ሙሴቬኒ አንባገነን ቢሆኑም ለሃገራቸው እድገት ብልሃት በተሞላበት መንገድ ሄደዋል።  ‘Think global, act local’ ነው ጫወታቸው። ‘ሞያ በልብ ነው’ ብለን ልንተረጉመው እንችላለን።
አባይን በፕሮፓጋንዳና በጩኸት ለመገደብ የተነሱት የኢትዮጵያ ገዢዎች ታዲያ ይህንን እያዩ እንኳን አልተማሩም።  አባይ ሲቀለበስ በላይቭ ቲቪ ማሳየት ከፕሮፓጋንዳነቱ ባሻገር ምንድነው ጥቅሙ?  ድርጊቱ ህልውናው በአባይ ወንዝ ላይ የሆነ ሕዝብን ለጦርነት መጋበዝ ይመስላል። ውግዘቱና ጫናው ሲበዛ ጉዳዩን ለማቆም ምክንያት ለመፍጠርም ያመቻል።
አለም አቀፉ ህብረተሰብ በ’ሕዳሴው ግድብ’ ጉዳይ ላይ ዝምታን ነው የመረጠው። ለዚህም ምክንያት አለው። ኢትዮጵያ ጨለማ ውስጥ ሆና ሌሎች ሃብትዋን ያላግባብ ሲጠቀሙ፤ ድልድሉ ትክክል እነዳልሆነ አለም ሳይረዳው ቀርቶ አይደለም። የመለስና ሙባረክ ፊርማ ሳይቀደድ የተጀመረው የአንድዮሽ ውሳኔም የት ተጀምሮ የት ላይ እንደሚያልቅ ያውቁታል። ለዚህም ይመስላል ለግድቡ የገንዘብም ሆነ የሞራል ድጋፋቸውን ሊነፍጉ የቻሉት።  የግድቡ ጅማሮ አንደኛ አመት ሲከበር የመንግስት ባለስልጣናት እና የውጭ ዲፕሎማቶች የእግር ኳስ ግጥሚያ እንደሚያደርጉ ፕሮግራም ወጥቶ ነበር። ዲፕሎማቶቹ ግን በስፍራው ሳይገኙ ቀሩ። ለ’ሕዳሴው’ ግድብ እውቅና በመስጠት የፖለቲካ ስህተት ላለመስራት የመከሩ ይመስላል።
ፕራግ፣ ቼክ ሪፐብሊክ፡ ግንቦት 24፣ 2005 ዓ.ም.

ተስፋዬ ዘነበ ከኖርዎይ

ከሳምንታት በፊት በልእለሀያሏ አሜሪካ በቦስተን ከተማ የደረሰውን በአሸባሪዎች ጥቃት ህይወታቸውን ላጡና ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው የሃገሪቱ ዜጎች በህዝብ ይሁንታ ስልጣን ላይ ያሉት ፕሬዘዳንት ባራክ ኦባማ በሰላማዊ ህዝብ ላይ ለደረሰው አደጋ ሀዘናቸውን ለመግለፅና የወንጀሉን ፈፃሚዎች በቁጥጥር ስር ለማዋል መመሪያ ሲሰጡ ሰዓታት እንዳልወሰደባቸው ስንመለከት ወራት አልተቆጠረም፡፡በመሰረቱ ይህንን ዘግናኝ ጥቃት የፈፀሙት ፅንፈኛ አክራሪዎች ብዙም ሳይቆዩ በሃገሪቱ የፀጥታ ሃይሎች ታድነው በአጭር ጊዜ ውስጥ መያዛቸው ለሕዝቡ ታማኝ የሆነ መንግስት ዜጎቹን ከጥቃት ለመታደግ ምን ያህል እረፍት እንደሌለው የሚያመላክት ነው፡፡
ከላይ እንደመነሻ ያነሳሁት ሃሳብ ለዛሬው ፅሁፌ እንደ መንደርደሪያ እንዲረዳኝ እንጂ እውነተኛው የዲሞክራሲያዊ ስርዓት አራማጆች ለዜጎቻችቸው የሚሰጡት ክብር የሚሳት ሆኖ አይደለው፡፡
ዲሞክራሲያዊ ስርዓትን ከቃል በዘለለ በተግባር የማያውቁት የወያኔ ቡድን፣ ፍትህና እርህትህ፣ ነፃነት ላጣው ሕዝብ ለውጥ ለማምጣት አጥንታችንን ከሰከስን ደማችንን አፈሰስን የሚሉት የዛሬዎቹ አምባገነን መሪዎች፣ የብሄር ብሄረሰቦችን መብት በኢትዮጲያ፣ ለማስፈን ደከመን ሰለቸን ሳንል ታተርን የሚሉን ጥቂት ዘረኛ ቡድኖች፣ ሃገሪቷንም ሕዝቧንም በሁለት አሃዝ በልማት አሳደግን ብለው ቀን ከሌት የሚደሰኩሩልን ጥቂት የዘረኛ ቡድን ሞኖፖሊስቶች፣ ከወረቀት ያልዘለለ የመናገርና አሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት አጎናፀፍን የሚሉን የዛሬዎቹ ተሸባሪ ሽብርተኞች በጀሌዎቻቸው የንፁሃን ደም ማስፈሰስ የሰነበቱበት የሃያ ሁለት አመት ተግባራቸው ቢሆንም በዚህ ሰሞን በባህር ዳር የተፈጸመውን ጅምላ ፍጅት በሙት መንፈስ አራማጁ በአቶ ሃይለማርያም ደሳለኝም ሆነ እሱን በሚመሩት የህውሃት ቡድኖች ምንም አለመባሉ ይህ እኩይ ሰርዓት ምን ያህል የሕዝብ ንቀት እንዳለበት ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ እውነት ነው፡፡
ስለዚህ ዘረኛ ስርዓት ብዙ ቢባልም በየጊዜው በህዝብ ላይ በሚያደርሳቸው ግድያዎችና የሰብአዊ መብት ጥሰቶች እንዲሁም በሃገር ላይ የሚያደርሳቸውን መጠነ ሰፊ ችግሮች በተመለከተ ከሃገርና ከሕዝብ ወገኖች ተቃውሞ ሲደርስበት ወይንም ሰራሗቸው እያለ ከሚመፃደቅባቸው ልማት ተብዬዎችን አስመልክቶ ከሚሰግድላቸው ምህራባዊያን ሃገሮችም ሆነ ከአበዳሪ አለም አቀፍ ተቋማት ጋር የሚወዛገበው በቁጥር ጨዋታ መሆኑ ስርዓቱ ምን ያህል ግትርና ሞራለ ቢስ መሆኑን አመላካች ነው፡፡
የወያኔ ዘረኛ ቡድን ከእድሜው መጀመሪያ ጀምሮ በዚች ሃገር ንፁሃን ዜጎች ላይ ለፈፀመው ፍጅት (ግድያዎች) አንድም ጊዜ በህግ የተጠየቀ አካል ካለመኖሩም ባሻገር የሟቾቹን ቁጥር በማሳነስ በዚህ አሸባሪ ስርዓት የተሰዉ ሰማህታት ቤተሰቦችንና ሕዝብን በመናቅ ሲሳለቁ መመልከት አዲስ ክስተት አይደለም፡፡ ሰሞኑን በባህር ዳር ከተማ የሆነውም ካለፈው ያልተማረው የወያኔ አምባገነን ቡድን የሆደበት የማደናገሪያ ተልካሻ ስልት መሆኑ ይህ ስርዓት በማን አለብኝነት የንፁሃንን ደም መጠጣቱ እንደቀጠለበት የሚያሳይ እውነት ነው፡፡
የጠለቀ ጥላቻ በዚች ታላቅ ሃገር ላይ ያለው ዘረኛው የህውሃት ቡድን ኢትዮጲያዊ መንፈስን ከሕዝብ ለመንጠቅ አንዱን ከአንዱ ለመለየት፣ በጎጥና በዘር እንዲሁም በእምነት ለመከፋፈል ሌት ከቀን ዘመኑን ሙሉ ለፍቷል፡፡ ሕዝብ አንድነትና ሕብረት እንዳይኖረው ውስጥ ውስጡን ሲያበጣብጥ፣ በዘር በተለከፉ ጀሌዎቹ አንዱን በአንዱ ላይ ለማስነሳት የሽብር ተግባር ሲከውኑ፣ በሌላ በኩል ደግሞ መጠሪያው የኢትዮጲያ ሕዝብ የሆነ ግን ደግሞ በሆድ አደር ካድሬዎች በሚመራው የሕዝብ ሃብት በሆነው ቴሌቪዥንና ሬድዮ ድርጅት በኩል የፈጠራ ፕሮፓጋንዳ በመፈብረክ የብሄር ብሄረሰቦች መብት መከበሩን ለማሳየት የሀሰት አታሞ ሲደልቅ ይታያል፡፡
በመሰረተ ሃሳብ ደረጃ ሸብር ማለት በማንም ይፈፀም በማን ሰላማዊውን ሕዝብ የሚያውክ፣ የተረጋጋ ህይወትን የሚረብሽ፣ የንፁሃንን ህይወት የሚቀጥፍ፣ ሕዝብን ያለፈቃዱ ከቀዬውና ከመንደሩ የሚያፈናቅል፣ የሰው ልጅ በተፈጥሮ የተቸረውን ነፃነት የሚቀማ፣ በሕዝብና በሃገር ላይ ጥፋትና ውድመትን የሚያስከትል . . . . .ወዘተ ከላይ በመጠኑ የተዘረዝሩት ሁሉ የዚህ ዘረኛ ቡድን መገለጫዎች መሆናቸው እንኳን ከሕዝብ ወገን ለተሰለፉ ነፃነት ናፋቂዎች ቀረቶ ስብእናቸውን ሸጠው ለሆዳቸው ላደሩት ለስርዓቱ ጀሌዎችም ቢሆን የሚጠፋቸው አይደለም፡፡ የሚገርመው ግን ይህው እኩይ ስርዓት በሕዝብና በሃገር ላይ የሚፈፅመውን በደልና ግፍ እንዲሁም ዜጎች የሚደርስባቸውን የመልካም አስተዳደር ችግርና የሰብአዊ መብት ጥሰትን በብእራቸው ነቅሰው የሚዘግቡትን ለሞያቸው ስነምግባር እንዲሁም ለሕዝብና ለሃገር ቅድሚያ የሚሰጡትን ጋዜጠኞች፣ በህግ አግባብ የመደራጀት መብታቸውን ተጠቅመው አማራጭ አሳብ በማስቀመጥ በሰላማዊ መንገድ የታገሉ የህዝብ ልጆችን፣ በተጨማሪም በሃገሪቱ ህገ-መንግስት በተደነገገው መሰረት የእምነት ነፃነታቸውን በዚህ ከፋፋይ ስርዓት ለመነጠቅ ፈቃደኛ ያልሆኑ፣ መብታቸውን ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መንገድ እየሞቱና እየተገረፉ ትግላቸውን ከአንድ አመት በላይ ያራመዱ የሙስሊሙ ማህበረሰብ የመፍትሄ አፈላላጊ መሪዎች፣ እነዚህ ከላይ ልዘረዝር የሞከርኳቸው ፍፁም ሰላማዊ የህብረተሰብ ክፍሎች በአሸባሪውና ተሸባሪው ዘረኛ ቡድን በተቆጣጠረው ነፃነት አልባው የፍትህ ስርዓት በአሸባሪነት ተፈርጀው በየማጎሪያው ይገኛሉ፡፡ ነገር ግን በሃገሪቱ የተለያዩ ክልሎች የንፁሃንን ህይወት በጠራራ ፀሃይ የሚነጥቀውና የሕዝብን ሰላማዊ ኑሮ ላለፉት ሃያ ሁለት አመታት የሚያውከው የህውሃት ዘረኛ ብድን በምግባር አሸባሪነቱ ከማንም የተሰወረ አይደለም፡

መቼም ህውሃት ውጥረት በነገሰበትና በደል ፅዋው ሞልቶ ተቃውሞ ሲበረታበት የሕዝቡን አመለካከት ለማስቀየር በስልጣን ዘመኑ ብዙ ተልካሻ ምክኒያቶችን ሲሰራ እንደ ነበረ ከማንም የተሰወረ አይደለም፡፡ በተለይ በአሁኑ ሰዓት የኢትዮጲያ አንድነት ለማፍረስና ለመበተን የስርዓቱ ሴረኝነት የበልጥ አግጥጦና አፍጦ የታየበት ጊዜ መሆኑ ግልፅ ነው፡፡ በተለይ በአማራው ብሄር ተወላጆች ላይ የከፈተው ጥቃት ኢትዮጲያን እንደ ሃገር ያላት ታላላቅ እሴቶች ለማጥፋት የታለመ መሆኑ ማስረጃ አይቻውም፡፡ ይህንን ተከትሌ የተነሳውን በአለም አቀፍ ደረጃ በነፃ ሃገር ላይ የመናገርና ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብታቸውን ተጠቅመው በሃገራችውና በወገናቸው ላይ የሚደርሰውን በደልና ግፍ የስቆጣቸው ኢትዮጲያዊያን ያሳዩት ተቃውሞና ሆነ ውግዘት አንገቱን ያስደፋው ዘረኛ ቡድን ሰሞኑን ደግሞ የሕዝብን መነሳሳት አቅጣጫ ለማስቀየር የመጣበት መንገድ ግርምትን የሚፈጥር ነው፡፡ በመሰረቱ የአሳ ግማቱ ከወደ አናቱ የሚለውን የአበው ብሂል ያስታውሰናል፡፡ እንደሚታወቀው የስርዓቱ ቁንጮዎች ከራስ ፀጉር እስከ እግር ጥፍር የሰጠሙበት ሙስና፣ ከድሃው ሕዝብ ጉሮሮ ነጥቀው የበለፀጉበት ሙስና፣ ገዢዎቻችን በስልጣን ዘመናቸው በደሃው ሕዝባችን ስም ለምነው ካገኙት ገንዘብ 11ቢሊዮን ዶላር በላይ ነጥቀው ያሸሹበት ሙስና፣ እነኚሁ ዘረኛ ገዢዎቻችን በኢፈርት(EFFORT-Endowment Fund For the Rehabilitation of Tigray)ስም የሃገሪቱን የንግድ እንቅስቃሴ እንደ ሸረሪት ድር ተብትበው የንግድና እንደስትሪውን ካፒታል ሳይጨምር ከ50ቢሊዮን ብር በላይ ቋሚ ሃብት ባለቤት የሆኑበት በጥቂት የህውሃት ሰዎች የሚሸከረከር ሙስና፣ ይህንንና እጅግ ብዙ የሙስና ንቅዘቶች ያለበት ስርዓት የተወሰኑ ጭፍሮቺን የውም በብሄር ለክቶ አስሮ ሙስናን አጠፋለሁ እያለ የዛን መከረኛ ሕዝብ ጆሮ ያደነቁራል፡፡
የአፍሪካን አንድነት ስንመሰርት ነፃ የነበርን ዜጎች ከአምሳ አመት በሗላ የሗሊት ተጉዘን በዘረኞች መዳፍ ስር ወድቆ መገኘት በዜግነት ክብራችን ላይ አሉታዊ ተፅኖ ያሳድራል ስለሆነም በአንድም ይሁን በሌላ መንገድ የሃገርና የሕዝብ ጥቃት የሚሰማን እስከ ወኔያችን እስከ ቤሄራዊ ስሜታችን ያለን እራሳችንን ሃገራችንን ከግዞት ነፃ ማውጣት ይጠበቅብናል፡፡
በተጨማሪም ግንቦት 17 ሰማያዊ ፓርቲ በጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ በመገኘት የሕዝብ ይሁንታ በሌለው ዘረኛ ቡድን የሚደርስብንን አፈናና የሰብአዊ መብት ጥሰት ለአለም አቀፉ ህብረተሰብ እናጋልጥ፡፡ ከአመት በላይ ድምፃችን ይሰማ እያልን በሰላማዊ መንገድ ስንታገል በአሸባሪነት ተፈርጀን መብታችንን የተነጠቅን የሙስሊሙ ማህበረሰብ ይህንን ሰልፍ በመቀላቀል ለለውጥ በአንድነት መቆማችንን እናረጋግጥ፡፡
ድል ለኢትዮጲያ ሕዝብ!!!!
ሞት ለወያኔ!!

ሰማያዊ ፓርቲ በመጪው እሁድ በሚጠራው ሰልፍ ላይ 100ሺህ ሰው ይገኛል ተብሎ ይጠበቃል

በመስከረም አያሌው


የፊታችን ግንቦት 25 ቀን 2005 ዓ.ም በሚካሄደው እና ሰማያዊ ፓርቲ በጠራው
ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ከ100 ሺህ በላይ ሰዎች ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የሰማያዊ ፓርቲ ፕሬዝዳንት ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት ለዝግጅት ክፍላችን
እንደገለፁት፤ ፓርቲው ባለፈው ግንቦት 17 ቀን 2005 ዓ.ም በአፍሪካ ህብረት ጽ/
ቤት ፊት ለፊት ሊያካሂድ የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ እንዲያራዝም መንግስት
በጠየቀው መሰረት የፊታችን እሁድ ያካሂዳል። መንግስት በፀጥታ እና ሰላም ማስከበር
ሂደት ከአቅም በላይ የሆነ ችግር ሲያጋጥመው ሰልፉን ለሌላ ጊዜ እንዲዛወር መጠየቅ
ይችላል የሚል ህግ በመኖሩ ሰልፉ ከአንድ ሳምንት በኋላ እንዲደረግ መወሰኑን
ፕሬዝዳንቱ ገልጸዋል።
ሰላማዊ ሰልፉን በአፍሪካ ህብረት በዓል ወቅት ማካሄድ የተፈለገው ኢትዮጵያ በአሉን
ስለምታዘጋጅ እና መንግስት ትኩረት ሰጥቶ የሚሰራው ስራ በመሆኑ የኢትዮጵያ
ህዝብና ሚዲያው እንዲሁም አለም አቀፍ ሚዲያዎች ስለሚሰሙት ጥያቄው ከፍ
ብሎ ይሰማል ከሚል አስተሳሰብ መሆኑን የገለፁት ፕሬዝዳንቱ፤ የሰላማዊ ሰልፉ ቀን
መራዘም ምንም የተለየ ነገር እንደማይፈጥር ገልፀዋል። “የችግሩ ባለቤትም ሆነ
መፍትሔ የኢትዮጵያ ህዝብ ነው። የሚጨቁነንም መንግስት እዚህ ነው ያለው” ያሉት
ፕሬዝዳንቱ፣ ሰልፉ በታሰበለት ቀን ቢካሄድ ጥሩ እንደነበር ገልፀው ቀኑ መቀየሩም ያን
ያህል ለውጥ እንደሌለው ተናግረዋል።
የሰላማዊ ሰልፉ በመራዘሙ በፊት ይሳተፋል ተብሎ ከታሰበው በላይ ሰው ይገኛል ተብሎ ይጠበቃል። ሰላማዊ ሰልፉን በህጉ
መሰረት ማስፈቀዱ እና ህዝቡም ጊዜ ወስዶ እንዲወያይበት በመደረጉ ከ100ሺ በላይ ሰዎች በሰልፉ ላይ ይገኛሉ ተብሎ
ይጠበቃል። በሰልፉ የሚነሱት አራት ጥያቄዎች በመሆናቸው ህዝቡ ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መንገድ እና የተነሱ ጥያቄዎችን
የተመለከተ ብቻ እንዲሆንም ፕሬዝዳንቱ አሳስበዋል። በሰላማዊ ሰልፉ ወቅትም የታሰሩ ፖለቲከኞች እና ጋዜጠኞች እንዲለቀቁ፣
የእስልምናን እምነት ነፃነት በመጠየቃቸው የታሰሩት የሙስሊም የመፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት እንዲፈቱ፣ የተፈናቀሉ ሰዎች
ወደሚኖሩበት አካባቢ በሰላም ተመልሰው ካሳ እና ድጎማ ተደርጎላቸው ህይወታቸውን እንዲቀጥሉ እንዲሁም የመልካም
አስተዳደር ችግሮች እንዲፈቱ እና በስራ አጥነት እና በሙስና ላይ መንግስት አፋጣኝ መፍትሔ እንዲፈልግ የሚሉ ጥያቄዎችን
አንግበው ሰላማዊ ሰልፉን እንደሚያካሂዱም ተገልጿል።
ከጠዋቱ 4 ሰዓት ጀምሮ ሰላማዊ ሰልፉ መነሻውን ግንፍሌ አካባቢ ከሚገኘው የፓርቲው ጽ/ቤት በማድረግ በአራት ኪሎ፣ ፒያሳ
እና ቸርቸል ጎዳና አልፎ እስከ ድላችን አደባባይ ወይም ኢትዮ-ኩባ ወዳጅነት አደባባይ የሚደረግ ሲሆን፤ በእለቱም አጠቃላይ
የሀገሪቱን ሁኔታ የሚገልፁ ንግግሮች እና መፈክሮች ይደረጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።¾
(ምንጭ ሰንደቅ ጋዜጣ የረቡዕ ሜይ 29 ዕትም)

ዲሞክራሲያዊ ስርዓትን ከቃል በዘለለ በተግባር የማያውቁት የወያኔ ቡድን፣ ፍትህና እርህትህ፣ ነፃነት ላጣው ሕዝብ ለውጥ ለማምጣት አጥንታችንን ከሰከስን ደማችንን አፈሰስን የሚሉት የዛሬዎቹ አምባገነን መሪዎች፣ የብሄር ብሄረሰቦችን መብት በኢትዮጲያ፣ ለማስፈን ደከመን ሰለቸን ሳንል ታተርን የሚሉን ጥቂት ዘረኛ ቡድኖች፣ ሃገሪቷንም ሕዝቧንም በሁለት አሃዝ በልማት አሳደግን ብለው ቀን ከሌት የሚደሰኩሩልን ጥቂት የዘረኛ ቡድን ሞኖፖሊስቶች፣ ከወረቀት ያልዘለለ የመናገርና አሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት አጎናፀፍን የሚሉን የዛሬዎቹ ተሸባሪ ሽብርተኞች በጀሌዎቻቸው የንፁሃን ደም ማስፈሰስ የሰነበቱበት የሃያ ሁለት አመት ተግባራቸው ቢሆንም በዚህ ሰሞን በባህር ዳር የተፈጸመውን ጅምላ ፍጅት በሙት መንፈስ አራማጁ በአቶ ሃይለማርያም ደሳለኝም ሆነ እሱን በሚመሩት የህውሃት ቡድኖች ምንም አለመባሉ ይህ እኩይ ሰርዓት ምን ያህል የሕዝብ ንቀት እንዳለበት ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ እውነት ነው፡፡
ስለዚህ ዘረኛ ስርዓት ብዙ ቢባልም በየጊዜው በህዝብ ላይ በሚያደርሳቸው ግድያዎችና የሰብአዊ መብት ጥሰቶች እንዲሁም በሃገር ላይ የሚያደርሳቸውን መጠነ ሰፊ ችግሮች በተመለከተ ከሃገርና ከሕዝብ ወገኖች ተቃውሞ ሲደርስበት ወይንም ሰራሗቸው እያለ ከሚመፃደቅባቸው ልማት ተብዬዎችን አስመልክቶ ከሚሰግድላቸው ምህራባዊያን ሃገሮችም ሆነ ከአበዳሪ አለም አቀፍ ተቋማት ጋር የሚወዛገበው በቁጥር ጨዋታ መሆኑ ስርዓቱ ምን ያህል ግትርና ሞራለ ቢስ መሆኑን አመላካች ነው፡፡
የወያኔ ዘረኛ ቡድን ከእድሜው መጀመሪያ ጀምሮ በዚች ሃገር ንፁሃን ዜጎች ላይ ለፈፀመው ፍጅት (ግድያዎች) አንድም ጊዜ በህግ የተጠየቀ አካል ካለመኖሩም ባሻገር የሟቾቹን ቁጥር በማሳነስ በዚህ አሸባሪ ስርዓት የተሰዉ ሰማህታት ቤተሰቦችንና ሕዝብን በመናቅ ሲሳለቁ መመልከት አዲስ ክስተት አይደለም፡፡ ሰሞኑን በባህር ዳር ከተማ የሆነውም ካለፈው ያልተማረው የወያኔ አምባገነን ቡድን የሆደበት የማደናገሪያ ተልካሻ ስልት መሆኑ ይህ ስርዓት በማን አለብኝነት የንፁሃንን ደም መጠጣቱ እንደቀጠለበት የሚያሳይ እውነት ነው፡፡
የጠለቀ ጥላቻ በዚች ታላቅ ሃገር ላይ ያለው ዘረኛው የህውሃት ቡድን ኢትዮጲያዊ መንፈስን ከሕዝብ ለመንጠቅ አንዱን ከአንዱ ለመለየት፣ በጎጥና በዘር እንዲሁም በእምነት ለመከፋፈል ሌት ከቀን ዘመኑን ሙሉ ለፍቷል፡፡ ሕዝብ አንድነትና ሕብረት እንዳይኖረው ውስጥ ውስጡን ሲያበጣብጥ፣ በዘር በተለከፉ ጀሌዎቹ አንዱን በአንዱ ላይ ለማስነሳት የሽብር ተግባር ሲከውኑ፣ በሌላ በኩል ደግሞ መጠሪያው የኢትዮጲያ ሕዝብ የሆነ ግን ደግሞ በሆድ አደር ካድሬዎች በሚመራው የሕዝብ ሃብት በሆነው ቴሌቪዥንና ሬድዮ ድርጅት በኩል የፈጠራ ፕሮፓጋንዳ በመፈብረክ የብሄር ብሄረሰቦች መብት መከበሩን ለማሳየት የሀሰት አታሞ ሲደልቅ ይታያል፡፡
በመሰረተ ሃሳብ ደረጃ ሸብር ማለት በማንም ይፈፀም በማን ሰላማዊውን ሕዝብ የሚያውክ፣ የተረጋጋ ህይወትን የሚረብሽ፣ የንፁሃንን ህይወት የሚቀጥፍ፣ ሕዝብን ያለፈቃዱ ከቀዬውና ከመንደሩ የሚያፈናቅል፣ የሰው ልጅ በተፈጥሮ የተቸረውን ነፃነት የሚቀማ፣ በሕዝብና በሃገር ላይ ጥፋትና ውድመትን የሚያስከትል . . . . .ወዘተ ከላይ በመጠኑ የተዘረዝሩት ሁሉ የዚህ ዘረኛ ቡድን መገለጫዎች መሆናቸው እንኳን ከሕዝብ ወገን ለተሰለፉ ነፃነት ናፋቂዎች ቀረቶ ስብእናቸውን ሸጠው ለሆዳቸው ላደሩት ለስርዓቱ ጀሌዎችም ቢሆን የሚጠፋቸው አይደለም፡፡ የሚገርመው ግን ይህው እኩይ ስርዓት በሕዝብና በሃገር ላይ የሚፈፅመውን በደልና ግፍ እንዲሁም ዜጎች የሚደርስባቸውን የመልካም አስተዳደር ችግርና የሰብአዊ መብት ጥሰትን በብእራቸው ነቅሰው የሚዘግቡትን ለሞያቸው ስነምግባር እንዲሁም ለሕዝብና ለሃገር ቅድሚያ የሚሰጡትን ጋዜጠኞች፣ በህግ አግባብ የመደራጀት መብታቸውን ተጠቅመው አማራጭ አሳብ በማስቀመጥ በሰላማዊ መንገድ የታገሉ የህዝብ ልጆችን፣ በተጨማሪም በሃገሪቱ ህገ-መንግስት በተደነገገው መሰረት የእምነት ነፃነታቸውን በዚህ ከፋፋይ ስርዓት ለመነጠቅ ፈቃደኛ ያልሆኑ፣ መብታቸውን ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መንገድ እየሞቱና እየተገረፉ ትግላቸውን ከአንድ አመት በላይ ያራመዱ የሙስሊሙ ማህበረሰብ የመፍትሄ አፈላላጊ መሪዎች፣ እነዚህ ከላይ ልዘረዝር የሞከርኳቸው ፍፁም ሰላማዊ የህብረተሰብ ክፍሎች በአሸባሪውና ተሸባሪው ዘረኛ ቡድን በተቆጣጠረው ነፃነት አልባው የፍትህ ስርዓት በአሸባሪነት ተፈርጀው በየማጎሪያው ይገኛሉ፡፡ ነገር ግን በሃገሪቱ የተለያዩ ክልሎች የንፁሃንን ህይወት በጠራራ ፀሃይ የሚነጥቀውና የሕዝብን ሰላማዊ ኑሮ ላለፉት ሃያ ሁለት አመታት የሚያውከው የህውሃት ዘረኛ ብድን በምግባር አሸባሪነቱ ከማንም የተሰወረ አይደለም፡

መቼም ህውሃት ውጥረት በነገሰበትና በደል ፅዋው ሞልቶ ተቃውሞ ሲበረታበት የሕዝቡን አመለካከት ለማስቀየር በስልጣን ዘመኑ ብዙ ተልካሻ ምክኒያቶችን ሲሰራ እንደ ነበረ ከማንም የተሰወረ አይደለም፡፡ በተለይ በአሁኑ ሰዓት የኢትዮጲያ አንድነት ለማፍረስና ለመበተን የስርዓቱ ሴረኝነት የበልጥ አግጥጦና አፍጦ የታየበት ጊዜ መሆኑ ግልፅ ነው፡፡ በተለይ በአማራው ብሄር ተወላጆች ላይ የከፈተው ጥቃት ኢትዮጲያን እንደ ሃገር ያላት ታላላቅ እሴቶች ለማጥፋት የታለመ መሆኑ ማስረጃ አይቻውም፡፡ ይህንን ተከትሌ የተነሳውን በአለም አቀፍ ደረጃ በነፃ ሃገር ላይ የመናገርና ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብታቸውን ተጠቅመው በሃገራችውና በወገናቸው ላይ የሚደርሰውን በደልና ግፍ የስቆጣቸው ኢትዮጲያዊያን ያሳዩት ተቃውሞና ሆነ ውግዘት አንገቱን ያስደፋው ዘረኛ ቡድን ሰሞኑን ደግሞ የሕዝብን መነሳሳት አቅጣጫ ለማስቀየር የመጣበት መንገድ ግርምትን የሚፈጥር ነው፡፡ በመሰረቱ የአሳ ግማቱ ከወደ አናቱ የሚለውን የአበው ብሂል ያስታውሰናል፡፡ እንደሚታወቀው የስርዓቱ ቁንጮዎች ከራስ ፀጉር እስከ እግር ጥፍር የሰጠሙበት ሙስና፣ ከድሃው ሕዝብ ጉሮሮ ነጥቀው የበለፀጉበት ሙስና፣ ገዢዎቻችን በስልጣን ዘመናቸው በደሃው ሕዝባችን ስም ለምነው ካገኙት ገንዘብ 11ቢሊዮን ዶላር በላይ ነጥቀው ያሸሹበት ሙስና፣ እነኚሁ ዘረኛ ገዢዎቻችን በኢፈርት(EFFORT-Endowment Fund For the Rehabilitation of Tigray)ስም የሃገሪቱን የንግድ እንቅስቃሴ እንደ ሸረሪት ድር ተብትበው የንግድና እንደስትሪውን ካፒታል ሳይጨምር ከ50ቢሊዮን ብር በላይ ቋሚ ሃብት ባለቤት የሆኑበት በጥቂት የህውሃት ሰዎች የሚሸከረከር ሙስና፣ ይህንንና እጅግ ብዙ የሙስና ንቅዘቶች ያለበት ስርዓት የተወሰኑ ጭፍሮቺን የውም በብሄር ለክቶ አስሮ ሙስናን አጠፋለሁ እያለ የዛን መከረኛ ሕዝብ ጆሮ ያደነቁራል፡፡
የአፍሪካን አንድነት ስንመሰርት ነፃ የነበርን ዜጎች ከአምሳ አመት በሗላ የሗሊት ተጉዘን በዘረኞች መዳፍ ስር ወድቆ መገኘት በዜግነት ክብራችን ላይ አሉታዊ ተፅኖ ያሳድራል ስለሆነም በአንድም ይሁን በሌላ መንገድ የሃገርና የሕዝብ ጥቃት የሚሰማን እስከ ወኔያችን እስከ ቤሄራዊ ስሜታችን ያለን እራሳችንን ሃገራችንን ከግዞት ነፃ ማውጣት ይጠበቅብናል፡፡

torsdag 11. april 2013

የትግራይ መምህራን እሮሯቸውን እያሰሙ ነው



(አብርሃ ደስታ ከመቀሌ)
በኢትዮዽያ ዩኒቨርስቲዎች እየሰለጠነ ያለው የሰው
ሃይል (ከምረቃ በኋላ) ብዙ ችግሮች
እንደሚፈታተኑት ይታወቃል። ከነዚህ ችግሮች አንዱ
‘ስራ ኣጥነት’ ነው። የስራ ኣጥነቱ ምንጭ ደግሞ
የፖለቲካ ሙስና ነው።
ሙሁራን ዜጎች የመንግስት ስራ (በሚፈልጉት
ዓይነት) የሚይዙት ባገኙት ውጤት ሳይሆን በዘመድ
ኣዝመድ ነው። የስራ ዕድገት (የደመወዝ ጭማሪ)
የሚያገኙት በስራ ብቃታቸው ሳይሆን በፖለቲካ
ኣመለካከታቸው (ለገዢው ፓርቲ ባላቸው ቅርበት
ወይ ታማኝነት) ነው።
ከዩኒቨርስቲ የተመረቁ ዜጎች የፖለቲካ ታማኝነታቸው ካላስመሰከሩ የኢኮኖሚ ሽብር ይደርሳቸዋል፤ ዕድገት ኣያገኙም
ወይም ከስራ እስከማባረር ድረስ ይደርሳሉ። ይህም ሁኖ ግን ብዙ ‘ስራ ኣጦች’ ኣሉ። (በኢትዮዽያ ዉስጥ ያለው ስራ
ኣጥነት ባብዛኛው በፍትሕ እጦት ምክንያት የሚፈጠር ነው።)
በትግራይ ክልል በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ መምህራን በፍትሕ ችግር፣ በኑሮ ውድነት እየተሰቃዩ ይገኛሉ። ክልሉ ለዜጎች
ስራ ፈጥርያለሁ ባይ ነው። ግን ብዙ መምህራን ቅሬታቸው እየገለፁ ይገኛሉ።
ባለፈው ሳምንት ነው። የትግራይ ክልል መንግስት ከመቐለ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር በትግራይ ላሉ መምህራን
በመማር ማስተማር (ፔዳጎጂ) ላይ ያተኮረ ስልጠና ለመስጠት ከመጋቢት 27 እስከ ሚያዝያ 1, 2005 ዓም ቀነ
ቀጠሮ ይዞ ነበር። ስልጠናው በሽረ፣ ዓድዋ፣ ውቅሮና ኣላማጣ ነበር እንዲካሄድ የታቀደው።
በስልጠናው የሚሳተፉ መምህራን 1615 ሲሆኑ ሁሉም በዲግሪ መርሃ ግብር የተመረቁ ናቸው። ስልጠናው
በሚሰጥበት ግዜ ታድያ ችግር ተፈጠረ። መምህራኖቹ ደስተኞች ኣይደሉም። “ ከስልጠናው በፊት ጥያቄዎቻችን
ይመለሱልን” ኣሉ። ለካ እነኚህ በዲግሪ የተመረቁ ሙሁራን የተቀጠሩት በዲፕሎማ ማዓርግ ነው። ደመወዛቸው
የሚከፈል በዲፕሎማ እርከን ሲሆን በወር 1233 (Monthly Gross Salary) ብር ብቻ ነው።
ይገርማል። እንዲህ ነው ምርቋኖቻችን ከዲግሪ ወደ ዲፕሎማ ሲያድጉ። 1233 ብር ግብር ሲቀነስበት ስንት
ይቀራል??? 1233 ብር የጫማ ዋጋ ነው ወይ ከቤት ኪራይ ኣያልፍም። በ1233 ብር ደመወዝ ምን ሊሰራ ይችላል?
(ኑሮ ውድነቱ ግምት ውስጥ ኣስገቡ)። ኣስተማሪዎቹ ዲግሪ ተምረው በዲፕሎማ ሲቀጠሩ ምን ዓይነት ሞራል
ይሰማቸው ይሆን? ምን በልተውስ ያስተምራሉ?
ሰው እንኳን ሳይበላ ሊያስተምር ሳይበላ መኖርም (መተኛት፣ መቀመጥ፣ መንቀሳቀስ) ኣይችልም። ስለዚህ በዚህ
ሞራልና ደመወዝ በኣግባቡ ሊያስተምሩ ኣይችሉም። አንዴ ተጎድተዋል። ተማሪዎችም ይጎዳሉ፣ ምክንያቱም በኣግባቡ
ሊማሩ ኣይችሉም። ሳይበሉ ስለ ፔዳጎጂ ሊማሩ??? ስለዚ ይሄ ኣካሄድ (መምህራን ደረጃቸው በመቀነስና በኣነስተኛ
ደመወዝ እንዲያስተምሩ ማስገደድ) ትውልድን ይገድላል።

ባጠቃላይ በኣስተማሪዎቹ ተቃውሞ ምክንያት ስልጠናው ኣልተሳካም። መንግስት ዲግሪ ለያዙ ሰዎች 1233 ብር ብቻ
ሲከፍል የባለስልጣናቱ ዘመዶች የሆኑ ግን (ዲግሪ እንኳ ሳይኖራቸው) በትእምት ከ100, 000 (መቶ ሺ) ብር በላይ
(አንዳንድ ተጨማሪ ጥቅማጥቅሞች ሳይጨምር) እንደሚከፈላቸው ይታወቃል።
እስከ መቼ ይሆን በእንደዚህ ዓይነት ኣድልዎና ጭቆና የምንኖረው? እኔ ግን ይሄን ኣሰራር ኣልፈልገውም፣
እቃወመዋለሁኝ።